አሰላለፍ እና ወቅታዊ መረጃዎች | ኮልፌ ቀራኒዮ ከ ወልቂጤ ከተማ

በተመሳሳይ ሰዓት ከሚደረጉ ጨዋታዎች አንዱ የሆነው እና በሰው ሰራሹ ሜዳ የሚከወነው ወደ ፕሪምየር ሊጉ የመግባት ዕድል ባላቸው ሁለት ቡድኖች መካከል የሚደረገውን ይህን ጨዋታ ወቅታዊ መረጃዎችን አጠናቅረናል፡፡

በአንፃሩ በጅማ አባ ጅፋር ሽንፈት አስተናግደው ወደ ዛሬው መርሐግብር ብቅ ያሉት የአሰልጣኝ መሀመድኑር ንማዎቹ ኮልፌ ቀራኒዮች ከባለፈው ጨዋታ ተሰላፊዎች ውስጥ ሀቢብ ከማልን በክንዱ ባየልኝ ብቻ በመተካት ለጨዋታው ዝግጁ ሆነዋል፡፡
በአሰልጣኝ ጳውሎስ ጌታቸው የሚመራው ወልቂጤ ከተማ ኢትዮ ኤሌክትሪክን ከረታበት ጨዋታ አንድም የአሰላለፍ ለውጥ ሳያደርግ ኮልፌ ቀራኒዮን ለመግጠም ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ይህን ጨዋታ ኢንተርናሽናል ዋና ዳኛ በላይ ታደሰ በመሀል ዳኝነት ይመሩታል፡፡

ቡድኖቹ የሚጠቀሙት የመጀመሪያ አሰላለፍ ይሄን ይመስላል፡፡

ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከ

25 ሀይማኖት አዲሱ
21 ተመስገን ዘውዱ
3 አቡበከር ከሚል
13 ፉዐድ ነስሩ
11 ኪሩቤል ወንድሙ
5 ፈቱ አብደላ
2 አቡበከር ሸሚል
7 አንዋር ዱላ
8 ደሳለኝ ወርቁ
10 ብሩክ ሙሉጌታ
16 ክንዱ ባየልኝ

ወልቂጤ ከተማ

1 ጀማል ጣሰው
12 ተስፋዬ ነጋሽ
15 ዮናስ በርታ
19 ዳግም ንጉሴ
3 ረመዳን የሱፍ
21 ሀብታሙ ሸዋለም
14 አብዱልከሪም ወርቁ
18 በኃይሉ ተሻገር
8 አቡበከር ሳኒ
7 አሜ መሐመድ
10 አህመድ ሁሴን