የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2008 የውድድር ዘመን ዛሬ ፍፃሜውን አግኝቷል

የኢትዮጵያ ፕሪሚር ሊግ የ2008 የውድድር ዘመን ዛሬ ሁለት ጨዋታ እና የመዝጊያ ስነስርአት አስተናግዶ ተጠናቋል፡፡ቅዱስ ጊዮርጊስም የኮከብነት ሽልማቶችን ጠራርጎ ወስዷል፡፡

08፡30 ላይ ደደቢት ሀዲያ ሆሳዕናን አስተናግዶ 4-1 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል፡፡ የደደቢትን የድል ግቦች ዳዊት ፍቃዱ ሁለት ፣ ሄኖክ ኢሳያስ እና ሳሚ ሳኑሚ ከመረብ አሳርፏል፡፡ ሁለት ግቦች ከመረብ ያሳረፈው ዳዊት ፍቃዱ የግብ መጠኑን 14 በማድረስ በከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ሰንጠረዡ ከቀድሞ የቡድን አጋሩ ታፈሰ ተስፋዬ በአንድ ግብ ብቻ በማነስ 2ኛ ደረጃ ይዞ አጠናቋል፡፡

PicsArt_1467229467033

10፡30 ላይ ሀዋሳ ከተማን ያስተናገደው ቻምፒዮኑ ቅዱስ ጊዮርጊስ 2-1 በማሸነፍ በድል ዋንጫውን ተቀብሏል፡፡ ሀዋሳ ከተማ ተጫዋቾች የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጫዋቾችን በክብር በማጀብ ወደ ሜዳ የገቡ ሲሆን ጫማውን እንደሚሰቅል ይፋ ያደረገው ሙሉጌታ ምህረት ከቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ስጦታ ተበርክቶለታል፡፡

PicsArt_1467229297598 PicsArt_1467229349821 PicsArt_1467229245330

የቅዱስ ጊዮርጊስን ግቦች አዳነ ግርማ እና ራምኬል ሎክ ከመረብ ሲሳረፉ የሃዋሳን ብቸኛ ግብ ሙሉጌታ ምህረት በፍፁም ቅጣት ምት ከመረብ በማሳረፍ የጨዋታ ዘመኑን በጎል ቋጭቷል፡፡

ውጤቱን ተከትሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ26 ጨዋታ 55 ነጥቦች በመሰብሰብ የውድድር ዘመኑን በቻምፒዮንነት አጠናቋል፡፡

PicsArt_1467229111703

ከጨዋታው በኋላ ለውድድሩ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የምስክር ወረቀት የተሰጠ ሲሆን ለውድድር ዘመኑ ኮከቦችም ሽልማት ተሰጥቷል፡፡

የውድድር ዘመኑ ኮከቦች ሽልማት የሚከተለውን ይመስላል፡-

ኮከብ አሰልጣኝ

ማርት ኑይ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) – 25,000 ብር

 

ኮከብ ተጫዋች

አስቻለው ታመነ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) -25,000 ብር

 

ኮከብ ግብ አግቢ

ታፈሰ ተስፋዬ (አዳማ ከተማ – በ15 ግቦች) – 25,000 ብር

 

ኮከብ ግብ ጠባቂ

ሮበርት ኦዶንካራ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) – 15,000 ብር

 

ኮከብ ረዳት ዳኛ

ክንዴ ሙሴ – 8000 ብር

 

ኮከብ ዳኛ

በላይ ታደሰ – 10,000 ብር

 

የስፖርታዊ ጨዋነት ተሸላሚ

መከላከያ የስፖርታዊ ጨዋነት ተሸላሚ ሆኗል፡፡

 

ልዩ ሽልማት

ሙሉጌታ ምህረት – 10,000 ብር

PicsArt_1467229397403PicsArt_1467229046931 PicsArt_1467226340133 PicsArt_1467225480464 PicsArt_1467225137475 PicsArt_1467225947243

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *