የኢትዮጵያ U-17 ዋንጫ ፡ ወደ ግማሽ ፍፃሜ የተሸጋገሩ ክለቦች ታውቀዋል

በኢትዮዽያ ከ17 አመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች የጥሎ ማለፍ ውድድር ትላንት በተደረጉ አራት የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ለግማሽ ፍፃሜ ያለፉ ቡድኖች ተለይተው ታውቀዋል፡፡

ቦዲቲ ላይ ወላይታ ድቻ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያደረጉት ጨዋታ በመደበኛ ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ በመጠናቀቁ በተሰጠው የመለያ ምት ወላይታ ድቻ 5-3 ማሸነፍ ችሏል፡፡

PicsArt_1467611085003

ጎፋ በሚገኘው የኤሌክትሪክ በተደረጉ ጨዋታዎች ኢትዮዽያ ቡና መከላክያን 1-0 ሲረታ ኤሌትሪክ በአፍሮ ፅዮን 2-1 ተሸንፏል፡፡

ሐዋሳ ላይ ቁጥሩ በርካታ የሆነ ተመልካች በተገኘበትና ማራኪ የኳስ እንቅስቃሴ በታየበት ጨዋታ ሁለቱን የዞን ቻምፒዮኖች ሀዋሳ ከተማ እና ደደቢትን አገናኝቶ ሀዋሳ ከተማዎች ከእረፍት መልስ ባስቆጠሩት ብቸኛ ጎል አሸንፈዋል፡፡

የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታዎች

ኢትዮጵያ ቡና ከ ወላይታ ድቻ

አፍሮ ፅዮን ከ ከሀዋሳ ከተማ

(የጨዋታዎቹ ቦታ፣ ቀን እና ሰአት ወደፊት ይገለፃል)

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *