በአአ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት በ11 ክለቦች መካከል ሲካሄድ የቆየው የ2008 የውድድር ዘመን የአአ ተስፋ ሊግ ዛሬ (ቅዳሜ) በአበበ በቂላ ስታድየም በድምቀት ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡
በመዝጊያው ስነስርአት ለአሸናፊዎቹ እና ለኮከቦች ሽልማት የተሰጠ ሲሆን ተሸላሚዎችም የሚከተሉት ናቸው፡-
ቻምፒዮን – የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ – የወርቅ ሜዳልያና የዋንጫ ተሸላሚ
2ኛ ደረጃ – ቅዱስ ጊዮርጊስ – የብር ሜዳልያ ተሸላሚ
3ኛ ደረጃ – ደደቢት – የነሀስ ሜዳልያ ተሸላሚ
ኮከብ ተጨዋች
ሚኪያስ ግርማ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) – 1500 ብር
ኮከብ ጎል አስቆጣሪ
ሞላለት ያለው (ኢትዮ ንግድ ባንክ 13 ጎል) – 1500 ብር
ኮከብ አሰልጣኝ
ግርማ ጸጋዬ (ኢትዮዽያ ንግድ ባንክ) – 1500 ብር
የስፖርታዊ ጨዋነት ዋንጫ – የሰውነት ቢሻው አካዳሚ