ወላይታ ድቻ የዝውውር ኢላማውን የከፍተኛ ሊግ እና ብሄራዊ ሊግ ተጫዋቾች ላይ አድርጓል

ወላይታ ድቻ ከዚህ ቀደም እንደተለመደው ሁሉ በዘንድሮው ክረምትም በተጫዋች ግዢ ላይ ከፍተኛ ገንዘብ እንደማያፈስ ታውቋል፡፡

ስማቸው ከአርባምንጭ ከተማ አሰልጣኝነት ጋር የተያያዙት አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪን በክለቡ ማቆየቱን ያረጋገጠው ወላይታ ድቻ ኮንትራታቸውን ያጠናቀቁ ተጫዋቾችን ውል በማደስ ላይ ትኩረቱን አድርጓል፡፡

ክለቡ በዚህ ሳምንት በውሰት የሚሰጡ እና የሚሰናበቱ እንዲሁም ከተስፋ ቡድን የሚያድጉ ተጫዋቾች ዙርያ ከውሳኔ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡

PicsArt_1468607556852

የዝውውር ገበያው ዋጋ ጣራ መንካት በወላይታ ድቻ የግዢ ፖሊሲ ላይ ለውጥ እንዳይኖር የሚያደርግ ሲሆን በፕሪሚየር ሊጉ ተጫዋቾች ላይ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ የከፍተኛ ሊግ እና ብሄራዊ ሊግ ተጫዋቾች ላይ ትኩረታቸውን አድርገዋል፡፡ የፕሪሚየር ሊግ ልምድ የሌላቸው ተጫዋቾችን በመሰብሰብ ጠንካራ ቡድን በመፍጠር የሚታወቁት አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ላይም እምነት አሳድሯል፡፡

አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ በክልል ከተሞች ተዘዋውረው የከፍተኛ ሊግ ጨዋታዎችን በመመልከት ተጫዋቾችን እየመለመሉ ሲሆን በሀምሌ ወር አጋማሽ የሚጀመረው የብሄራዊ ሊግ ማጠቃለያ ውድድር ላይ ትኩረት አድርገው ለመስራት እንደተዘጋጁ ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *