ድሬዳዋ ከተማ ከግማሽ ደርዘን በላይ ተጫዋቾችን ለማስፈረም ከስምምነት ደርሷል

አዲሱ የድሬዳዋ ከተማ አሰልጣኝ ዘላለም ሽፈራው በይፋ ከተሾሙ ወዲህ በተጫዋች ግዢ ላይ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡

አሰልጣኙ የከፍተኛ ሊግ ጨዋታዎችን ተዟዙረው የተመለከቱ ሲሆን ትኩረታቸውን የሳቧቸው 4 ተጫዋቾችን የግላቸው አድርገዋል፡፡ በቀጣዮቹ ቀናትም የተጫዋቾቹ ማንነት ይታወቃሉ ተብሏል፡፡

ድሬዳዋ የዳሽኑን ግብ ጠባቂ ቢንያም ሀብታሙ ወደ ትውልድ ከተማው ሲመልስ ከአሰልጣኙ ጋር በሲዳማ ቡና አብረው የሰሩት አሳምነው አንጀሎ እና ዘነበ ከበደ ለክለቡ ለመፈረም ተስማምተዋል፡፡ ከአዳማ ከተማ የተለቀቀው ቢንያም አየለም ወደ ድሬዳዋ ከተማ የሚመልሰውን ዝውውር ለማድረግ ተቃርቧል፡፡

PicsArt_1468903110908

ብርቱካናማዎቹ ካስፈረሟቸው ተጫዋቾች ባሻገር ውሉን የጨረሰው ዳዊት እስጢፋኖስን ኮንትራት ለማደስ በድርድር ላይ የሚገኝ ሲሆን በአጭር ጊዜ ኮንትራት ድሬዳዋን የተቀላቀለው ዮርዳኖስ አባይ በቀጣዩ አመትም ከክለቡ ጋር ለመቆየት በመደራደር ላይ ይገኛል፡፡

አሁን ባገኘነው መረጃ ደግሞ ዳዊት እስጢፋኖስ ከክለቡ ጋር የመቀጠሉ ነገር ያበቃለት እንደሆነ ከክለቡ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *