U17 ፕሪሚየር ሊግ ፡ በማጠቃለያው 4ኛ ቀን ሲዳማ ቡና ድል ቀንቶታል

የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ፕሪሚየር ሊግ የማጠቃለያ ውድድር 4ኛ ቀኑን ይዟል፡፡ ዛሬ በምድብ ሀ በተደረጉ 2ኛ ጨዋታዎችም ሲዳማ ቡና ድል ሲቀናው ከፍተኛ ግምት አግኝቶ የነበረው ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡

08:00 ላይ አዲስ አበባ ከተማን የገጠመው ሲዳማ ቡና 1-0 አሸንፏል፡፡ የሲዳማ ቡናን ብቸኛ የማሸነፍያ ጎል ከመረብ ያሳረፈው ፋሲል ዳግም ነው፡፡

10:00 ላይ የምድባቸውን የመጀመርያ ጨዋታ ያሸነፉት ሀዋሳ ከተማ እና ሐረር ሲቲ ተገናኝተው ያለ ግብ ጨዋታውን ፈጽመዋል፡

 

ከ2 ጨዋታዎች በኋላ የደረጃ ሰንጠረዦች ይህን ይመስላል፡-

PicsArt_1468957718793 PicsArt_1468957647352

የነገ ጨዋታዎች

08:00 ወላይታ ድቻ ከ ደደቢት

10:00 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ አዳማ ከተማ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *