ሀዋሳ ከተማ ለ17 አመት በታች ቡድኑ የማበረታቻ ሽልማት አበረከተ

በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የተዘጋጁትን ከ17 አመት በታች ውድድሮች በማሸነፍ ስኬታማ የውድድር ዘመን ያሳለፈው ሀዋሳ ከተማ ትላንት በሴንትራል ሆቴል ለቡድኑ አባላት የማበረታቻ ሽልማት አበርክቷል፡፡

የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ደቡብ-ምስራቅ ዞን እና የማጠቃለያ ውድድሩን እንዲሁም የጥሎማለፉን በበላይነት ላጠናቀቁት የቡድኑ ተጫዋቾች በየደረጃው ለያንዳንቸው ከ4,000-5000 ብር የተበረከተላቸው ሲሆን ለአሰልጣኝ ተመስገን ዳና የ 5500 እንዲሁም ለረዳታቸው እስራኤል ጊና 5000 ብር ፣ ለህክምና ባለምያው ዘሪሁን ዳዊት 4500 ብር እና ለቡድን መሪው ጠሀ አህመድ 4500 ብር ተበርክቶላቸዋል፡፡

ከ100ሺህ ብር በላይ ወጪ በተደረገበትን የማበረታቻ ሽልማት ያበረከቱት የሀዋሳ ከተማ ም/ከንቲባ እና የክለቡ ፕሬዝዳንት አቶ ታምሩ ታፌ እና የሀዋሳ ከተማ ወጣቶች እና ስፖርት ሀላፊና የክለቡ ምክትል ፕሬዝደንት አቶ ታሪኩ ኡጋሞ ናቸው፡፡

PicsArt_1471265313030

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *