ሉሲዎቹ የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ዝግጅታቸውን ጀምረዋል

የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ከመስከረም 1 ጀምሮ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የመጀመርያው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ዝግጅቱን ትላንት በድሬዳዋ ጀምሯል፡፡

በአሰልጣኝ መሰረት ማኒ የሚመሩት ሉሲዎቹ ባሳለፍነው ሳምንት የ31 ተጨዋቾች ምርጫ ይፋ ከተደረገ በኋላ ቅዳሜ ድሬዳዋ ገብተው መቀመጫቸውን ትሪያንግል ሆቴል በማድረግ ትላንት የመጀመርያ ልምምዳቸውን የሰሩ ሲሆን ዛሬም በድሬዳዋ ስታድየም ሁለተኛ ቀን ልምዳቸውን አከናውነዋል፡፡

PicsArt_1471870940137

ተጨዋቾቹ ከእረፍት እንደመመለሳቸው ወደ አካል ብቃታቸው እንዲመለሱ በማሰብ በቀን ሁለት ጊዜ ጠንከር ያለ ልምምድ ሰርተዋል፡፡

ይህ የልምምድ መርሃ ግብር ለአንድ ሳምንት የሚቀጥል ሲሆን የወዳጅነት ጨዋታዎች እና ቀለል ያሉ ልምምዶች የሚቀጥሉ ይሆናል፡፡

PicsArt_1471871069758

ከ31 ተጫዋቾች ስብስብ መካከል ሀብታም እሸቱ እና ቅድስት ቦጋለ ባጋጠማቸው የግል ጉዳይ ከቡድኑ ውጪ ሆነዋል፡፡

ሉሲዎቹ እስከ ጳጉሜ 1 ድረስ በድሬዳዋ የሚቆዩ ሲሆን 6 ተጨዋቾች ተቀንሰው 23 ተጫዋቾች ጳጉሜ 3 ቀን 2008 ወደ ዩጋንዳ ያመራሉ፡፡

PicsArt_1471870897980

ከዛሬው ልምምድ ፍጻሜ በኋላ ቡድኑን ወደ ሆቴል የሚያደርሰው ተሽከርካሪ ከ45 ደቂቃ በላይ በመዘግየቱ በቡድኑ አባላት ላይ መጉላላት የደረሰ ሲሆን በቀጣይ እንዲህ አይነት ክፍተቶች ሊታረሙ ይገባል መልክታችን ነው፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *