በፊፋ የሃገራት ሰንጠረዥ ኢትዮጵያ 4 ደረጃዎችን አሻሽላለች

 ዋልያዎቹ | 05-01-2009 

ፊፋ በየወሩ በሚያወጣው የሃገራት ደረጃ ኢትዮጵያ 126ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡

ኢትዮጵያ ባለፈው ወር በወጣው ደረጃ 130ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣ የነበረ ሲሆን 4 ደረጃዎችን በማሻሻል ወደ 126ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡

የአለም ሃገራትን ሰንጠረዥን አሁንም በመሪነት ስትቀጥል የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳልያ ባለቤቷ ብራዚል 4 ደረጃ አሻሽላ 4ኛ ላይ ተቀምጣለች፡፡ ከአፍሪካ ሀገራት ደግሞ አይቮሪኮስት የአልጄሪያን ቦታ ስትወስድ ኢትዮጵያ 39ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡

 

የአፍሪካ ሃገራት ደረጃ (በቅንፍ የተቀመጠው የአለም ሃገራት ደረጃቸው ነው)

1. ኮት ዲቯር (34)

2. አልጄርያ (35)

3. ሴኔጋል (39)

4. ቱኒዚያ (42)

5. ጋና  (43)

6. ኮንጎ ዲ.ሪ. (51)

7. ግብፅ (53)

8. ኮንጎ ብራዛቪል (54)

9. ማሊ (55)

10. ሞሮኮ (58)

.

.

.

39. ኢትዮጵያ (123)

 

የአለም ሃገራት ደረጃ

1 አርጀንቲና

2 ቤልጅየም

3 ጀርመን

4 ብራዚል

4 ኮሎምቢያ

6 ቺሊ

7 ፖርቱጋል

8 ፈረንሳይ

9 ኡራጓይ

10 ዌልስ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *