‘ሚቾ’ ለዩጋንዳ የአፍሪካ ዋንጫ ቡድን 40 ተጫዋቾችን ጠርተዋል

ጋቦን በጥር 2017 ለምታስተናግደው የቶታል አፍሪካ ዋንጫ ዝግጅት እንዲረዳቸው የዩጋንዳ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሰርዮቪች ሚሉቲን ‘ሚቾ’ 40 ተጫዋቾችን ዛሬ ይፋ አድርገዋል፡፡ ሰርቢያዊው አሰልጣኝ በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከሚጫወቱ አራት ዩጋንዳዊያን መካከል ሶስቱን በቡድናቸው ስብስብ ውስጥ አስገብተዋል፡፡

የቅዱስ ጊዮርጊሶቹ ሮበርት ኦዶንካራ፣ አይዛክ ኢዜንዴ እና ያስር ሙገርዋን ሲጠሩ ለጅማ አባ ቡና በቋሚነት ላይ በመጫወት የሚገኘው አማካዩ ክሪዝስቶ ንታሚቢ ከምርጫው ውጪ ሆኗል፡፡ ኦዶንካራ የፕሪምየር ሊጉ መክፈቻ ሃገሩ በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ በነበረባት ጨዋታ ምክንያት ሳይሰለፍ ቢቀርም ቅዱስ ጊዮርጊስ ደደቢትን እና መከላከያን በረታበት ጨዋታዎች የፈረሰኞቹን ግብ ጠብቋል፡፡ በተሰለፈባቸው ሁለት ጨዋታዎችም ግቦች አልተቆጠሩበትም፡፡

ያስር ሙገርዋ በሊጉ አንድም ጨዋታ ያላደረገ ሲሆን በሚቾ ስብስብ ውስጥ መካተት ችሏል፡፡ በካፍ ግሎ በአፍሪካ የሚጫወት የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ዕጩ ውስጥ የገባው ዴኒስ ኦኒያን፣ አጥቂው ፋሩክ ሚያ ሌሎች የተካተቱ ተጫዋቾች ናቸው፡፡ ሚቾ ስለምርጫው እንዳሉት ከሆነ ሁሉም ተጫዋቾች የመጨረሻ 23ቱ ውስጥ ለመግባት ዕኩል ዕድል አላቸው፡፡

img_0558

“የ40 ተጫዋቾች ስብስብ የያዘ ቡድን አሳውቀናል፡፡ 5 ግብ ጠባቂዎች፣ 12 ተከላካዮች፣ 15 አማካዮች እና 8 አጥቂዎች የመጨረሻዎቹ የ23ቱ ስብስብ ውስጥ ቦታ ለማግኘት እና ዩጋንዳን ከ39 ዓመታት በኃላ በጋቦን 2017 የአፍሪካ ዋንጫ ለመወከል ይፎካከራሉ፡፡” ይላሉ ሚቾ፡፡

ሚቾ አያይዘውም ብድናቸው ልምድ ያላቸው እና ወጣት ተጫዋቾችን መያዙን ይገልፃሉ፡፡ “የመረጥነው ልምድ ያላቸው እና የዩጋንዳ እግርኳስ የወደፊት ተስፋዎች የሆኑ ወጣት ተጫዋቾች ድብልቅ ነው፡፡ ማንም በስጦታ መልክ ይሁን በማንኛው መንገድ በአፍሪካ ዋንጫው ቡድን ውስጥ ቦታ አይሰጠውም፡፡ አሁን ቆጣሪው ከዜሮ ነው የሚጀምረው፡፡ ሁሉም ተጫዋቾች በጤናማ ፉክክር የመጨረሻዎቹ 23ቱን የሚቀላቀሉ ይሆናል፡፡”

img_0414

ሙሉ ስብስብ

 

ግብ ጠባቂዎች

ዴኒስ ኢኒያጎ

ሮበርት ኦዶንካራ

ጀማል ሳሊም

ኢስማኤል ዋቴንጋ

ቤንጃሚን ኦቻን

 

ተከላካዮች

ዴኒስ ኢጉማ

ጆሴፍ ንሱቡጋ

ኒኮላስ ዋዳዳ

ጆሴፍ ኦቻያ

ሻፊክ ባታምቡዚ

አይዛክ ኢዜንዴ

ሙሩሺድ ጁኮ

ሮናልድ ሙኪቢ

ቲሞቲ አዋኒ

ሪቻርድ ካሳጋ

ካሊድ ልዋሊዋ

ራሺድ ቶሃ

 

አማካዮች

ካሊድ አዉቾ

ቶኒ ማዊጄ

ሃሰን ዋሳዋ

ማይኪ አዚራ

ጂኦፍሪ ኪዚቶ

ኬዚሮን ኪዚቶ

ሙዛሚል ሙትያባ

ያስር ሙገርዋ

ጁማ ሳዳም

ሞሰስ ኦሎያ

ዊሊያም ሉዋጋ ኪዚቶ

ጎድፍሬ ዋሉሲምቢ

ፓል ሙኩርዚ

ማርቲን ኪዛ

ታቡ ቪታሊስ

 

አጥቂዎች

ፋሩክ ሚያ

ጅዮፍሪ ማሳ

ጅዮፍሪ ሴሬንኩማ

መሃመድ ሻባን

ዩኑስ ሴንታሙ

ዴሪክ ንሲባምቢ

ኢድሪሳ ሉቤጋ

ኢሪሳ ሲኪሳምቡ

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *