ፍፁም ገ/ማርያም ልምምድ ጀመረ

የቅዱስ ጊዮርጊሱ አጥቂ ፍፁም ገ/ማርያም ለተጨማሪ ህክምና አሜሪካ ተጉዞ ከ26 ቀናት የአሜሪካ ቆይታ በኋላ ወደ ክለቡ ተመልሶ ልምምድ መጀመሩ ተነግሯል፡፡ 

በከባድ ጉዳት ከሜዳ ርቆ የሰነበተው የቀድሞ የሙገር ሲሚንቶ አጥቂ መመለስ በኡመድ ኡኩሪ ላይ ጥገኛ ለሆነው የአሰልጣኝ ማርቲን ኑይ የአጥቂ ክፍል አማራጭ ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በተመሳሳይ ለረጅም ጊዜያት ጉዳት ላይ የነበረው አማካዩ ተስፋዬቦ አለባቸው ወደ ልምምድ መመለሱ ተነግሯል፡፡

©ሶከር ኢትዮጵያ