በሴቶች ጥሎማለፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ ያለፉ 4 ክለቦች ታውቀዋል

የኢትዮጵያ ሴቶች ጥሎማለፍ ውድድር 2ኛ ዙር ጨዋታዎች ትላንት ተደርገው ወደ ሩብ ፍጻሜ ያለፉት 4 ክለቦች ታውቀዋል፡፡

አበበ ቢቂላ ላይ በ08:00 አዳማ ከተማ ከ ቅድስት ማርያም ዩኒቨርሲቲ ያደረጉት ጨዋታ በአዳማ 3-1 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡ ቀጥሎ በተደረገው ጨዋታ ደግሞ ጌዲኦ ዲላ በአስገራሚ ጉዞው በመቀጠል ልደታ ክፍለ ከተማን 5-1 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል፡፡

አአ ስታድየም ላይ በ09:00 ሊካሄድ የነበረው የድሬዳዋ ከተማ እና ኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርተት አካዳሚ ጨዋታ ድሬዳዋ በቦታው ባለመገኘቱ ምክንያት ሳይካሄድ ቀርቷል፡፡ ለአካዳሚም ፎርፌ ተሰጥቷል፡፡ ቀጥሎ በተካሄደው ጨዋታ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ ቦሌ ክፍለከተማን 1-0 በማሸነፍ ሌላው ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀለ ቡድን ሆኗል፡፡

የ2ኛው ዙር ቀጣይ ጨዋታዎች የካቲት 21 ተካሂደው ወደ ሩብ ፍጻሜው የሚያልፉ ክለቦች ይለያሉ፡፡

 

2ኛ ዙር

የካቲት 17 ቀን 2009

ድሬዳዋ ከተማ 0-3 ኢ.ወ.ስ. አካዳሚ (ፎርፌ)

ቦሌ 0-1 ንፋስ ስልክ ላፍቶ

አዳማ ከተማ 3-1 ቅድስት ማርያም

ልደታ 1-5 ጌዲኦ ዲላ

 

ማክሰኞ የካቲት 21 ቀን 2009

09:00 ጥረት ከ ኢትዮጵያ ቡና (አአ ስታድየም)

11:30 ደደቢት ከ ሲዳማ ቡና (አአ ስታድየም)

08:00 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ አርባምንጭ ከተማ (አበበ

ቢቂላ)

10: 00 መከላከያ ከ ሀዋሳ ከተማ (አበበ ቢቂላ)

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *