ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 0-0 የወልድያ | የአሰልጣኞች አስተያየት

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የወልድያ የሁለተኛው ዙር መክፈቻ ጨዋታ ያለግብ ተጠናቋል ። የአቻ ውጤቱን ተከትሎም የቡድኑ አሰልጣኞች ስለጨዋታው ያላቸውን አስተያየት ለጋዜጠኞች እንደሚከተለው  ገልፀዋል ።

አሰልጣኝ ሲሳይ ከበደ – ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

” በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ጥሩ መንቀሳቀስ ችለን ነበር ። ወደጎል ባንቀይራቸውም ብዙ የግብ ዕድሎችንም ፈጥረን ነበር ። በሁለተኛውም አጋማሽም እንዲሁ በመልሶ ማጥቃት እድሎችን ለመፍጠር ሞክረን ነበር ። ሆኖም ግን መጠቀም አልቻልንም ። ቢሆንም ሶስት ተከታታይ ጨዋታዎችን ተሸንፈን እንደመምጣታችን ውጤቱ በጣም ጥሩ ባይባልም ከሽንፈቱ ስነልቦና ከመውጣት አንፃር ጥሩ የሚባል ነው ። በቀጣይ ያስፈረምናቸው እና ለዚህ ጨዋታ ያልደረሱልንን ተጨዋቾች ከቀጣዩ ሳምንት ጀምረን በመጠቀም ቡድኑን ወደ መልካም ውጤት ለማምጣት ይምንሰራ ይሆናል ።”

አሰልጣኝ ንጉሴ ደስታ –  ወልድያ

” የዛሬው ጨዋታ ተመጣጣኝ ነበር ። ወደ ጎል በመድረስ ግን እኛ የተሻልን ነበርን ። እንቅስቃሴያችንም ከምንጊዜውም በላይ የተሻለ ነበር ። ጎል የማግባት  አቅማችን አሁንም ትንሽ ወረድ ያለ ነው ። በዚህ በኩል ብዙ መስተካከል የሚገባቸው ነገሮች አሉ ። ያገኘናቸውን ኳሶች አለመጠቀማችንም ዋጋ እያስከፈለን ነው ። አንድ ሁለት የሚሆኑ አዲስ ተጨዋቾችን ለማስገባት ሞክረናል ሆኖም የነበረን ጊዜ አጭር በመሆኑ ችግሮቻችንን ሙሉ ለሙሉ አልቀረፍንም ። ቡድኑ የመጀመሪያ ዕቅዱ በሊጉ መቆየት እንደመሆኑ መጠን በመከላከሉ ከሚያሳየው ጥንካሬ በተጨማሪ በተጋጣሚዎች ላይ ብልጫ ለመውሰድ እና ጎሎችን ለማስቆጠር ጠንክረን መስራት ይኖርብናል ። “

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *