የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 29ኛ እና 30ኛ ሳምንት መርሀ ግብሮች በብሄራዊ ቡድን ዝግጅት ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ የኢንተርናሽናል ጨዋታ እና ላለመውረድ የሚጫወቱ ቡድኖች በተመሳሳይ ጊዜ ጨዋታ እንዲያደርጉ በሚል ላልታወቀ ጊዜ መሸጋገራቸው የሚታወስ ነው፡፡
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ዛሬ ይፋ ባደረገው መርሀ ግብር መረረት የ29ኛ ሳምንት መርሀ ግብር መቼ እና የት እንደሚደረግ ታውቋል፡፡ አጓጊ በሆነው ላለመውረድ በሚደረገው ፉክክር የሚሳተፉት ክለቦች የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች በተመሳሳይ ሰአት የሚካሄዱ መሆናቸውን ተከትሎ የኤሌክትሪክ እና ወልድያ ጨዋታ ከተለመደው አአ ስታድየም ወጥቶ ሰበታ ላይ የሚካሄድ ይሆናል፡፡
መርሀ ግብሩ የሚከተለውን ይመስላል፡-