የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ የምድብ ድልድል ወጣ

የአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን በየአመቱ የሚያዘጋጀው የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ (ሲቲ ካፕ) በመጪው እሁድ ይጀመራል፡፡

ካስትል ቢራ ስፖንሰር ያደረገው ይህ ውድድር የምድብ ድልድል ዛሬ ይፋ የተደረገ ሲሆን 6 የመዲናዋ ክለቦች እና 2 ተጋባዥ ክለቦች በሁለት ምድብ ተከፍለዋል፡፡

የምድብ ድልድሉ ይህንን ይመስላል…

ምድብ አንድ ፡- ኢትዮጵያ ቡና ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ አዳማ ከነማ እና ደደቢት

ምድብ ሁለት ፡- ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ ዳሽን ቢራ ፣ መከላከያ እና መብራት ኃይል

ውድድሩ እሁድ መስከረም 25 ቀን 2007 ዓ.ም ኢትዮጵያ ቡና ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በአዲስ አበባ ስታድየም በሚያደርጉት ጨዋታ ይከፈታል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *