ሀዲያ ሆሳዕና ከአማካዩ ጋር ተለያይቷል

ሀድያ ሆሳዕና በአንድ ዓመት ውል ተቀላቅሎ የነበረው ማሊያዊ አማካይ ለክለቡ ጨዋታ ሳያደርግ በስምምነት ከክለቡ ጋር ተለያይቷል።
በክረምቱ የዝውውር መስኮት ለሀዲያ ሆሳዕና ለመጫወት ፊርማውን አኖሮ የነበረው የቀድሞ የስታደ ደ ማሊያን ፣ ላፊያ እና ዩኤስ ኤም አልጀርስ ተጫዋች የነበረው ማሊያዊው አማካይ ሴኮ ኮናቴ ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር ያለው ውል ስለመቋረጡ ተሰምቷል።
በክረምቱ የዝውውር መስኮት በቁጥር አነስተኛ ዝውውር ለፈፀሙት ሀዲያ ሆሳዕናዎች ለአንድ ዓመት የሚያቆየውን ውል የተፈራረመው ማሊያዊው አማካይ ከሳምንታት ቆይታ በኃላ ከቡድኑ ጋር ያለው ውል መቋረጡ ተሰምቷል።