ሽመልስ በቀለ ከዋልያዎቹ ጋር የመጀመርያ ልምምዱን ሰርቷል ፤ ጌታነህ ዛሬ አአ ይገባል

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ከሌሶቶ ብሄራዊ ቡድን ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ ዝግጅቱን ቀጥሏል፡፡

የዋልያዎቹን የመጨረሻ የማጣርያ ጨዋታ በአምበልነት የመራው ሽመልስ በቀለ ትላንት አዲስ አበባ የገባ ሲሆን በዛሬው እለትም ከቡድኑ ጋር የመጀመርያ ልምምዱን ሰርቷል፡፡ ጌታነህ ከበደ ደግሞ ዛሬ አዲስ አበባ የሚገባ ሲሆን ነገ ከቡድኑ ጋር ይቀላቀላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የብሄራዊ ቡድኑ ጥሪ ከደረሳቸው 25 ተጫዋቾች መካከልም 24ቱ ልምምዳቸውን ሲሰሩ በጠባብ ሜዳ ውስጥ ክፍተት የማግኘት እና ጎል የማስቆጠር ልምምዶች እንዲሁም  ለሁለት ተከፍለው መጫወት የዛሬ የልምምዳቸው አካል ነበር፡፡

PicsArt_1464599764215

ብሄራዊ ቡድኑ ኢንተርናሽናል የአቋም መለኪያ ጨዋታ ያላገኘ ሲሆን በነገው እለት ጠዋት ከኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ እንደሚያደርጉ ታውቋል፡፡

አሰልጣኝ ገብረመድን እስካሁን ባለው ዝግጅት በጣም ደስተኛ እንደሆኑና በቡድኑ ቅንጅትና እንቅስቃሴ እንደተገረሙ እና ጥሩ ስራ እየሰሩ መሆኑን ለሶከር ኢትዮዽያ ተናግረዋል፡፡

ዋልያዎቹ በዕለተ ረቡዕ ወደ በደቡብ አፍሪካ ትራንዚት አድርገው ሌሶቶ የሚያመሩ ሲሆን እሁድ ግንቦት 28 ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

PicsArt_1464599888028

ሶከር ኢትዮዽያ ነገ በብሄራዊ ቡድኑ ዝግጅት ዙርያ የተጨዋቾችን እና አሰልጣኞች አስተያየት ይዛ የምትቀርብ ይሆናል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *