የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን ለመልሱ ጨዋታ በአዳማ ዝግጅት ጀምሯል

በዛምቢያ አስናጋጅነት ለሚካሄደው የ2017 የአፍሪካ ከ20 አመት በታች ዋንጫ ማጣርያ ጋናን የሚገጥመው የኢትየጵያ ከ20 አመት ብሄራዊ ቡድን በአዳማ ከትሞ ዝግጅቱን ጀምሯል ፡፡

በመጀመርያው ጨዋታ አአ ስታድየም ላይ በአሜ መሃመድ ግቦች ተግዞ 2-1 ያሸነፈው ወጣት ቡድኑ ከሰኞ ጀምሮ ልምምዱን ይጀምራል ቢባልም ዘግይቶ ትላንት በአዳማ አበበ በቂላ ስታድየም ጀምሯል፡፡

ብሄራዊ ቡድናችን የዛሬውን የልምምድ ፕሮግራም ረፋድ ላይ ለማደረግ ቢያስብም ሜዳው በመያዙ ምክንያት ከ10:00 በኋላ ልምምዳቸውን ለመስራት ተገደዋል፡፡

PicsArt_1464803424875

በዛሬው ልምምዳቸው 20 ተጨዋቾች የተገኙ ሲሆን የውህደት ስራዎች እና በጠባብ ቦታ ውስጥ ኳስን ተረጋግቶ የመቀባበል ልምምድ ሲሰሩ ለማየት ችለናል፡፡

ከጉዳት ጋር በተያያዘ የጅማ አባቡናዎቹ ኪዳኔ አሰፋና ሱራፌል አወል መጠነኛ ጉዳት አጋጥሟቸው በዛሬው ልምምድ ያልተገኙ ሲሆን የጅማ አባ ቡናው ጀሚል የፓስፖርት ጉዳይ ለመጨረስ አዲስ አበባ በመሄዱ በዛሬው ልምምድ ላይ አልተገኘም፡፡

አዳማ ለዝግጅት የተመረጠው በጋና የሚጠብቃቸውን ሞቃታማ አየር ከወዲሁ ለመላመድ  እንደሆነ ሲታወቅ ወደ ጋና እስኪሄዱ ድረስም በዚሁ እንደሚቆዩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

PicsArt_1464803481548

የተቀነሱ እና የተጨመሩ ተጫዋቾች

በጋና የመጀመርያው ጨዋታ ላይ ከነበሩት 23 ተጨዋቾች መካከል የወጣቶች አካዳሚው ግብ ጠባቂ ጆቤድ ፣  የደደቢቱ ቢንያም አበራ እና የዩኒቲ ጋምቤላው ጋድ ጋትኮች የተቀነሱ ሲሆን በምትካቸው የመከላከያው ቴዎድሮስ ታፈሰ ፣ የጅማ አባ ቡናው ጀሚል ያዕቆብ ፣ የአሶሳ ከተማው ዮሴፍ መርጋ ቡድኑን ተቀላቅለዋል፡፡

PicsArt_1464803564069

የአቋም መለክያ ጨዋታ

ከ20 አመት በታች ቡድኑ ከማሊ አቻው ጋር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ እንዳገኘ አስታውቆ የነበረ ቢሆንም ከስምምነት ላይ መድረስ እንዳልቻሉ ተነግሯል፡፡ በምትኩም ከኢትዮዽያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ጋር ለመጫወት ቅድመ ሁኔታዎችን እያመቻቹ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል ።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *