የኢትዮዽያ ከ20 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን በማሊ በሰፊ የግብ ልዩነት ተሸነፈ

ለአፍሪካ ከ20 አመት በታች ዋንጫ ማጣርያ የመልስ ጨዋታ በዝግጅት ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን ዛሬ ከማሊ ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 5-0 ተሸንፏል፡፡

ሁለቱም ቡድኖች በ90 ደቂቃ ውስጥ ሙሉ 23 ተጨዋቾቻቸውን በዘጠና የተጠቀሙ ሲሆን የኢትዮዽያ ብሔራዊ ቡድን በመጀመርያው አጋማሽ በጋናው ጨዋታ ላይ ቋሚ ተሰላፊ የነበሩትን ተጠቅሟል፡፡ በዚህ ክፍለ ጊዜም 2-0 እየተመራወደ መልበሻ ክፍል አምርቷል፡፡

በሁለተኛው አጋማሽ የተጫወቱት ቀሪ የቡድን አባላት ሶስት ግቦች አስተናግደው ጨዋታው በማሊ 5-0 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡

ብሄራዊ ቡድኑ ነገ በኛ ሰአት አቆጣጠር 5:45 ላይ ወደ ጋና የሚያቀና ይሆናል፡፡

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *