ከፍተኛ ሊግ ፡ ወልድያ ወሳኝ ድል ሲያስመዘግብ መድን ደረጃውን ከፍ አድርጓል

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ 21ኛ ሳምንት ዛሬም ቀጥሎ ሲውል ወልድያ አሸንፏል፡፡ አማራ ውሃ ስራ እና ኢትዮጵያ መድንም ወደ መሪዎቹ የተጠጉበትን ድል አስመዝግበዋል፡፡

ከፍተኛ ግምት አግኝቶ የነበረው የወልድያ እና መቀለ ከተማ ጨዋታ በወልድያ አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡ ያሬድ ሀሰን የመታው ኳስ በተከላካዮች ተጨርፎ የድል ግብ ሆኗል፡፡

ኢትዮጵያ መድን ሰሜን ሸዋ ደብረብርሃንን አስተናግዶ 1-0 አሸንፏል፡፡ ጨዋታው ሊጠናቀቅ ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩ የመድንን ወሳኝ የድል ግብ ከመረብ ያሳረፈው የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ አምበል ሳምሶን ሙሉጌታ ነው፡፡

 

21ኛው ሳምንት የተመዘገቡ ውጤቶች እና ቀጣይ ጨዋታዎች ይህንን ይመስላሉ፡-

 

ምድብ ሀ

ቅዳሜ ሰኔ 11 ቀን 2008

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 0-1 ጅማ ከተማ

ተምኪን ፋቱ

ወልድያ 1-0 መቐለ ከተማ

ያሬድ ሀሰን

አማራ ውሃ ስራ 2-0 አክሱም ከተማ

ኤርሚያስ ፍስሃ (2)

ኢትዮጵያ መድን 1-0 ሰሜንሸዋ ደብረብርሃን

ሳምሶን ሙሉጌታ

ቡራዩ ከተማ X ወሎ ኮምቦልቻ

በጣለው ዝናብ ምክንያት ሜዳው በመጨቅየቱ ለነገ 04:00 ተዛውሯል

ሰበታ ከተማ 3-1 ኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት

ናትናኤል ጋንጂላ (2) ፣ ሄኖክ |

እሁድ ሰኔ 12 ቀን 2008

09፡00 ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከ ባህርዳር ከተማ (አዲግራት)

ማክሰኞ ሰኔ 14 ቀን 2008

09፡00 ፋሲል ከተማ ከ ሱሉልታ ከተማ (ጎንደር)

09:00 አዲስ አበባ ፖሊስ ከ ሙገር ሲሚንቶ (አበበ ቢቂላ)

PicsArt_1466260681293

ምድብ ለ

አርብ ሰኔ 10 ቀን 2008

ፌዴራል ፖሊስ 1-0 ጂንካ ከተማ

ሊቁ ታደሰ

ወራቤ ከተማ X ሻሸመኔ ከተማ

ጨዋታው በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ተቋርጧል፡፡

አርሲ ነገሌ 1-0 ድሬዳዋ ፖሊስ

ቱፋ ተሺቴ

ናሽናል ሴሜንት 2-1 ባቱ ከተማ

ካሌብ አበበ (2) | በሃይሉ ሀምዛ

 

ማክሰኞ ሰኔ 14 ቀን 2008

09፡00 ጅማ አባ ቡና ከ ነቀምት ከተማ (ጅማ)

 

ረቡዕ ሰኔ 15 ቀን 2008

09:00 ሀላባ ከተማ ከ አዲስ አበባ ከተማ (ሀላባ)

09:00 ነገሌ ቦረና ከ ደቡብ ፖሊስ  (ነገሌ ቦረና)

PicsArt_1466263915419

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *