ፕሪሚየር ሊግ ፡ ሲዳማ ቡና ድል ሲቀናው መከላከያ እና ባንክ ነጥብ ተጋርተዋል

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 24ኛ ሳምንት ዛሬም ቀጥሎ ሲውል ሲዳማ ቡና ድል ቀንቶታል፡፡ መከላከያ እና ባንክ ደግሞ ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል፡፡

09:00 ላይ ሲዳማ ቡናን ያስተናገደው ደደቢት 1-0 ተሸንፏል፡፡ በጣለው ዝናብ ምክንያት ሜዳው ውሃ በመያዙ ኳስ እንደልብ ማንሸራሸር ባልተቻለበት ጨዋታ ጥቂት የግብ ሙከራዎች ተስተናግደዋል፡፡

በሁለተኛው አጋማሽ አንዱአለም ንጉሴ በጥሩ ሁኔታ ያመቻቸለትን ኳስ ተጠቅሞ በረከት አዲሱ የሲዳማ ቡናን የድል ግብ ከመረብ አሳርፏል፡፡

PicsArt_1466359600291

11:30 ላይ የተገናኙት መከላከያ እና ንግድ ባንክ ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል፡፡

ግብ በማስቆጠር ቅድሚያውን የያዙት ንግድ ባንኮች ሲሆኑ የፊሊፕ ዳውዚን መቀጣት ተከትሎ የመጀመርያ አሰላለፍ ውስጥ የተካተተው ዳኛቸው በቀለ በግንባሩ በመግጨት አስቆጥሯል፡፡

PicsArt_1466359550000

ከግቡ መቆጠር በኋላ የተሻለ መንቀሳቀስ የቻሉት መከላከያዎች በሳሙኤል ታዬ አማካኝነት አቻ ሆነዋል፡፡ ከግብ ክልሉ የወጣው ፌቮ ኳሱን በአግባቡ ባለማራቁ ያገኘውን ኳስ ሳሙኤል በቀጥታ መትቶ ከመረብ አሳርፏል፡፡

ሁለተኛው አጋማሽ የተቀዛቀዘ እንቅስቃሴ የታየበት ሲሆን ይህ ነው የሚባል የግብ ሙከራ ሳይታይ ጨዋታው 1-1 ተጠናቋል፡፡

PicsArt_1466359473907

የደረጃ ሰንጠረዥ

PicsArt_1466354209283

ከፍተኛ ግብ አግቢዎች

PicsArt_1466273665397

ቀጣይ የ24ኛ ሳምንት ጨዋታዎች

ሰኞ ሰኔ 13 ቀን 2008

09፡00 አርባምንጭ ከተማ ከ ሀዋሳ ከተማ (አርባምንጭ)

09:00 ኤሌክትሪክ ከ ሀዲያ ሆሳዕና (አአ ስታድየም)

10፡00 ኢትዮጵያ ቡና ከ ድሬዳዋ ከተማ (አበበ ቢቂላ-ዝግ ስታድየም)

11፡30 ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ዳሽን ቢራ (አአ ስታድየም)

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *