ታፈሰ ተስፋዬ እና የፕሪሚየር ሊጉ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2008 የውድድር ዘመን ትላንት ፍጻሜውን ሲያገኝ ታፈሰ ተስፋዬ በ15 ግቦች የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብርን ተጎናፅፏል፡፡ የፕሪሚየር ሊጉን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች ዝርዝር እና ተያያዥ እውነታዎችን እንደሚከተለው አቅርበንላችኋል፡፡

የመጀመርያው ሽልማት

የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በውድድር ዘመኑ በከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት የሚያጠናቅቁ ተጫዋቾችን በመሸለም እውቅና መስጠት የጀመረው በ1977 ነበር፡፡ የመጀመርያው ተሸላሚም የቅዱስ ጊዮርጊሱ ሙሉጌታ ከበደ ነበር፡፡

ከአንድ ጊዜ በላይ የኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ክብር ያገኙ ተጫዋቾች

ታፈሰ ተስፋዬ ለ5 ጊዜያት ያህል ከፍተና ግብ አስቆጣሪ ሆኖ በማጠናቀቅ ተወዳዳሪ አልተገኘለትም፡፡ ታፈሰ በኤሌክትሪክ (1) ፣ ኢትዮጵያ ቡና (2) እና በአዳማ ከተማ (1) ማልያዎች ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆኖ አጠናቋል፡፡ ዮርዳኖስ አባይ ፣ ሙሉጌታ ከበደ እና አህመድ ጁንዲ 3 ጊዜ ሲያገኙ ጌቱ ከበደ ፣ አሰግድ ተስፋዬ ፣ አዳነ ግርማ እና ጌታነህ ከበደ 2 ጊዜ አግኝተዋል፡፡

በአንድ የውድድር ዘመን በርካታ ግብ

ዮርዳኖስ አባይ በ1993 የውድድር ዘመን 24 ግቦች አስቆጥሮ እስካሁን ያልተሰበረ ሪኮርድ ይዟል፡፡ ታፈሰ ተስፋዬ በ2001 የውድድር ዘመን ፣ አዳነ ግርማ በ2004 የውድድር ዘመን 23 ግቦች በማስቆጠር ይከተላሉ፡፡

PicsArt_1467293794826

በተከታታይ ያሸነፉ ተጫዋቾች

ዮርዳኖስ አባይ ለ3 ተከታታይ አመታት በኮከብ ግብ አግቢነት በማጠናቀቅ ቀዳሚው ተጫዋች ነው፡፡ ዮርዳኖስ በ1993 ፣ 94 እና 95 በከፍተኛ ግብ አግቢነት አጠናቋል፡፡ ሙሉጌታ ከበደ ፣ ጌቱ ከበደ ፣ አሰግድ ተስፋዬ እና ታፈሰ ተስፋዬ ለ2 ተከታታይ አመታት ተሸልመዋል፡፡

አህመድ ጁንዲ

የቀድሞው የምድር ባቡር ኮከብ 3 ጊዜ በኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ቢያጠናቅቅም ሁሉንም ሽልማቶች በአስገራሚ ሁኔታ ከሌሎች ጋር ተጋርቷል፡፡ አህመድ በ1988 ከአሰግድ ተስፋዬ ጋር ፣ በ1995 ከዮርዳኖስ አባይ ጋር ፣ በ1996 ከታፈሰ ተስፋዬ እና መሳይ ተፈሪ ጋር ኮከብነት ሽልማቱን ተጋርቷል፡፡

ብቸኛው የውጭ ዜጋ

በ2007 የውድድር ዘመንን በኮከብ ግብ አግቢነት ያጠናቀቀው ናይጄርያዊው ሳሙኤል ሳኑሚ ይህንን ክብር የወሰደ ብቸኛው የውጭ ዜጋ ነው፡፡ የደደቢቱ ሳኑሚ በ22 ግቦች የውድድር ዘመኑን በኮብ ግብ አግቢነት ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡

በርካታ ኮከብ ግብ አስቆጣሪ የያዙ ክለቦች

የቅዱስ ጊዮርጊስ ተጫዋቾች 10 ጊዜያት ያህል በኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ሲያጠናቅቁ ፣ የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋቾች 7 ፣ የኤሌክትሪክ እና ምድር ጦር ተጫዋቾች 4 ጊዜ አሸንፈዋል፡፡

ለትውስታ

ፕሪሚየር ሊጉ በአዲስ መልክ ከተዋቀረበት 1990 ጀምሮ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን ያጠናቀቁት የሚከተሉት ናቸው

1990. ሀሰን በሽር (ኢትዮጵያ መድን) – 8

1991. በረከት ሀጎስ (ሀዋሳ ከተማ) – 8

1992. ስንታየሁ ጌታቸው (ቅዱስ ጊዮርጊስ) – 8

1993. ዮርዳኖስ አባይ (ኤሌክትሪክ) – 24

1994. ዮርዳኖስ አባይ (ኤሌክትሪክ) – 20

1995. ዮርዳኖስ አባይ (ኤሌክትሪክ/ኢትዮጵያ ቡና) – 14

አህመድ ጁንዲ (ምድር ባቡር) – 14

1996. መሳይ ተፈሪ (አርባምንጭ ጨጨ) – 13

ታፈሰ ተስፋዬ (ኤሌክትሪክ) – 13

አህመድ ጁንዲ (ምድር ባቡር) – 13

1997. መዳህኔ ታደሰ (ትራንስ ኢትዮጵያ) – 18

1998. ታፈሰ ተስፋዬ (ኢትዮጵያ ቡና) – 21

1999. (በውድድር ዘመኑ አጋማሽ 10 ክለቦች አቋርጠው እስኪወጡ ድረስ ታፈሰ በ11 ግብ ይመራ ነበር፡፡ በወቅቱ ለኮብ ግብ አግቢ ሽልማት አልተሰጠም)

2000. ሳላዲን ሰኢድ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) – 21

2001. ታፈሰ ተስፋዬ (ኢትዮጵያ ቡና) – 23

2002. ታፈሰ ተስፋዬ (ኢትዮጵያ ቡና) – 21

2003. አዳነ ግርማ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) – 20

ጌታነህ ከበደ (ደደቢት) – 20

2004. አዳነ ግርማ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) – 23

2005. ጌታነህ ከበደ (ደደቢት) – 22

2006. ኡመድ ኡኩሪ (ቅዱስ ጊዮርጊስ) – 16

2007. ሳሙኤል ሳኑሚ (ደደቢት) – 22

2008. ታፈሰ ተስፋዬ (አዳማ ከተማ) – 15

PicsArt_1467274709245PicsArt_1467293886777
PicsArt_1467293844804 PicsArt_1467293816907 PicsArt_1467293485143 PicsArt_1467293750663 PicsArt_1467293550693 PicsArt_1467293613355 PicsArt_1467293678809

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *