ከፍተኛ ሊግ ፡ የወራቤ ከተማ እና አዲስ አበባ ከተማ ጨዋታ ለሌላ ጊዜ ተሸጋገረ

በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ትላንት ሊደረግ የነበረው የወራቤ ከተማ እና አዲስ አበባ ከተማ ጨዋታ በጣለው ዝናብ ምክንያት ለዛሬ 04:00 መተላለፉ ይታወሳል፡፡ ነገር ግን ዝናቡ እስከ ረፋድ በመቀጠሉና ሜዳው ባለመድረቁ ጨዋታው ሳይደረግ ቀርቷል፡፡

ጨዋታው ዛሬ እንዲካሄድ በወራቤ ከተማ በሚገኝ ሌላ ሜዳ ለማድረግ ቢሞከርም በተመሳሳይ በመጨቅየቱ ዋናው የወራቤ ሜዳ እስኪደርቅ ለመገበቅ ተገዷል፡፡ ሆኖም ሜዳው ባለመድረቁ ጨዋታው ለሌላ ጊዜ ተሸጋግሯል፡፡

PicsArt_1468583565923

በቀጣዮቹ ቀናት የወራቤ ሜዳ ሁኔታ ታይቶ ጨዋታውን ለማድረግ የማያስችል ከሆነ ጨዋታው በሀዋሳ አልያም ባቱ ሊደረግ ይችላል ተብሏል፡፡ ይህም ሁለቱ ክለቦች ከጅማ አባ ቡና እና ጂንካ ከተማ ጋር ሰኞ እንዲያደርጉ የወጣላቸው ተስተካካይ ጨዋታ ወደ ሌላ ጊዜ እንዲሸጋገር ያደርገዋል፡፡

ሁለቱ ክለቦች በ3 ነጥቦች ልዩነት 2ኛ እና 3ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡ ሲሆን ይህን ጨዋታ ሳይጨምር አዲስ አበባ ከተማ 3 ፣ ወራቤ ከተማ ደግሞ 1 ተስተካካይ ጨዋታ ይቀራቸዋል፡፡

ትላንት የተመዘገቡት ውጤቶች እና የደረጃ ሰንጠረዥ ይህንን ይመስላል፡-

ሀሙስ ሐምሌ 7 ቀን 2008

ምድብ ሀ

አክሱም ከተማ 1-1 ሰሜንሸዋ ደብረብርሃን

ወልድያ 2-1 ወሎ ኮምቦልቻ

ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ 1-2 ሙገር ሲሚንቶ

ኢትዮጵያ መድን 2-2 ሱሉልታ ከተማ

ቡራዩ ከተማ 0-1 ፋሲል ከተማ

ሰበታ ከተማ 2-1 አዲስ አበባ ፖሊስ

PicsArt_1468506625383

ምድብ ለ

ጅማ ከተማ 3-1 ሻሸመኔ ከተማ

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 1-3 ጂንካ ከተማ

ነገሌ ቦረና 2-0 ባቱ ከተማ

ሀላባ ከተማ 1-0 ናሽናል ሴሚንቶ

ጅማ አባ ቡና 2-0 ፌዴራል ፖሊስ

ድሬዳዋ ፖሊስ 1-2 ደቡብ ፖሊስ

PicsArt_1468509421707

ያልተደረጉ ጨዋታዎች

አርሲ ነገሌ ከ ነቀምት ከተማ

(ለእሁድ ተሸጋግሯል)

አማራ ውሃ ስራ ከ ኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት

(ለሌላ ጊዜ ተላልፏል )

ባህርዳር ከተማ ከ መቐለ ከተማ

(ለሌላ ጊዜ ተላልፏል)

ወራቤ ከተማ ከ አአ ከተማ

(ለሌላ ጊዜ ተላልፏል)

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *