ደደቢት የቻምፒዮንስ ሊግ ተጋጣሚውን አወቀ
የካፍ ቻምፒዮንስ ሊግ የ2014 የውድድር ዘመን ድልድል ይፋ ሲሆን ደደቢት ተጋጣሚውን አውቋል።
የአምናው የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ቻምፒዮን በቅድመ ማጣርያው ከዛንዚባሩ ሻምፒዮን ኬ ኤም ኤም ኬ ጋር ተደልድሏል፡፡ የመጀመርያው ጨዋታን ከሜዳው ውጪ የሚያደርገው ደደቢት የመልሱን በሜዳው የሚያከናውን መሆኑ ወደ ተከታዩ ዙር ለማለፍ ምቹ አጋጣሚ ይፈጥረለታል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ ድልድል በፅፅር ቀለል ያለ ቢመስልም የብዙዎችን ትኩረት የሳበው ይህንን ዙር ካለፈ የቱኒዚያውን የ2013 ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ አሸናፊ ስፖርቲ ሴፋክሲያን ማግኘቱ ነው፡፡ የቱኒዚያው ክለብ ባለፈው የውድድር ዘመን ቅ/ጊዮርጊስን በኮንፌዴሬሽን ዋንጫ የምድብ ጨዋታ ላይ አዲስ አበባ ላይ በደጋፊው ፊት 3-1 ማሽነፉ ይታወሳል፡፡
©Soccer Ethiopia
ተዛማጅ ፅሁፎች
“በጀመርነው ፎርማት ውድድራችንን እንቀጥላለን” መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ
ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2014 ኮከቦቹን በሸራተን አዲስ ሆቴል ዛሬ አመሻሹን ይሸልማል፡፡ ከሽልማት ስነ ሥርዓቱ አስቀድሞ የፕሪምየር ሊጉ አክሲዮን ማኅበር...
ጦሩ ከአጥቂው ጋር ተለያይቷል
ከወራት በፊት መከላከያን የተቀላቀለው ጊኒያዊው አጥቂ ውሉን በስምምነት ቀዶ ዛሬ ወደ ሀገሩ አምርቷል። የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ነገ ከመከፈቱ በፊት በርካታ...
አቡበከር ናስር የጎፈሬ ብራንድ አምባሳደር ሆኖ ነገ ይፈራረማል
ሀገር በቀሉ የትጥቅ አምራች ተቋም ጎፈሬ የወቅቱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ኮከብ አቡበከር ናስር የብራንድ አምባሳደሩ ለማድረግ ነገ ስምምነት ይፈፅማል። የሀገር...
ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾቹ ጋር በስምምነት ተለያይቷል
ከደቂቃዎች በፊት ከታፈሰ ሰለሞን ጋር መለያየቱን የዘገብነው ኢትዮጵያ ቡና ከተጨማሪ ሦስት ተጫዋቾች ጋር በተመሳሳይ ለመለያየት ከስምምነት ላይ መድረሱ ታውቋል። ኢትዮጵያ...
ኢትዮጵያ ቡና ከአማካይ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል
የዝውውር መስኮቱ ሊከፈት ሰዓታት በሚቀሩበት ወቅት ኢትዮጵያ ቡና ከአንድ ተጫዋቹ ጋር ለመለያየት ተስማምቷል። ኢትዮጵያ ቡና በቀጣይ ዓመት ራሱን አጠናክሮ ለመቅረብ...
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ውላቸው ከዛሬ ጀምሮ ይቋረጣል
አሠልጣኝ ካሣዬ አራጌ ቀሪ የአንድ ዓመት ውል እያላቸው በውሉ ላይ በተቀመጡት ዝርዝሮች መሠረት ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ከዛሬ ጀምሮ እንደሚለያዩ ሥራ-አስኪያጁ...