U17 ፕሪሚየር ሊግ : በማጠቃለያው የ7ኛ ቀን ውሎ መከላከያ ድል ቀንቶታል

የኢትዮጵያ ከ17 አመት ፕሪሚየር ሊግ የምድብ ጨዋታዎች ቀጥለዋል፡፡ ዛሬ 7ኛ ቀኑን በያዘው ውድድር መከላከያ ድል ሲቀናው ንግድ ባንክ ከ ወላይታ ድቻ አቻ ተለያይተዋል፡፡

08:00 ላይ በተደረገው ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ወላይታ ድቻ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡ ሁለቱ ቡድኖች የማለፍ ተስፋቸውን ለማለምለም ይህንን ጨዋታ ማሸነፍ ቢጠበቅባቸውም ሳይሸናነፉ ጨዋታቸውን ፈጽመዋል፡፡

10:00 ላይ መከላከያ ደደቢትን 2-1 በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ የማለፍ ተስፋውን አለምልሟል፡፡

የመከላከያን ሁለቱንም የድል ግቦች ዮሐንስ ደረጄ ከመረብ ሲያሳርፍ የደደቢትን ጎል በዛብህ ኩምሳ አስቆጥሯል፡፡

ዮሃንስ ዛሬ ያስቆጠራቸውን ግቦች ጨምሮ የግብ መጠኑን 4 በማድረስ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በመምራት ላይ ይገኛል፡፡

 

የነገጨዋታዎች

08:00 አአ ከተማ ከ ሀዋሳ ከተማ

10:00 ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ሲዳማ ቡና

 

ኮከብ ጎል አስቆጣሪዎች

4 ዮሃንስ ደረጄ (መከላከያ)

3 የኋላሸት ፍቃዱ (አዳማ ከተማ)

3 እንደልቡ ደሴ (ቅዱስ ጊዮርጊስ)

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *