U17 ፕሪሚየር ሊግ ፡ በማጠቃለያው 8ኛ ቀን ውሎ ሀዋሳ ከተማ አሸንፏል

በኢትየጵያ ከ17 አመት በታች የማጠቃልያ ውድድር 8ኛ ቀን ውሎ በተደረጉ ጨዋታዎች ሀዋሳ ከተማ ድል ሲቀናው ሲዳማ እና ጊዮርጊስ ነጥብ ተጋርተዋል፡፡

08:00 ላይ ሀዋሳ ከተማ አዲስ አበባ ከተማን 2-0 በማሸነፍ የማለፍ ተስፋውን አስፍቷል፡፡ የሀዋሳን የድል ጎሎች ገብረመስቀል ደበሌ እና ያሬድ መሀመድ አስቆጥረዋል፡፡

10:00 ላይ በተካሄደው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ሲዳማ ቡና ካለግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡

የዚህ ምድብ አላፊ እስካሁን ያልተለየ ሲሆን ወደ ግማሽ ፍጻሜ የሚያልፉትን ክለቦች ለመለየት የመጨረሻውን ጨዋታ መጠበቅ ግድ ይላል፡፡

PicsArt_1469291312149

በተያያዘ ዜና ትላንት የተካሄደው የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ እና ወላይታ ድቻ ጨዋታ ከተጠናቀቀ በኋላ ከስፖርታዊ ጨዋነት መርህ ውጪ የዕለቱ ዳኞች ላይ በፈፀሙት ያልተገባ ባህሪ ምክንያት ሦስት የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ተጨዋቾች ላይ ቅጣት ተላልፎባቸዋል፡፡ ውሳኔው የተላለፈው በፍርዱ ተካልኝ ፣ ሄኖክ ሩጋ እና ምስክር ታገል ላይ ሲሆን የአንድ አመት ቅጣትና የ5000 ብር የገንዘብ ቅጣት በዲሲፒሊን ኮሚቴው ተወስኖባቸዋል፡፡

ውድድሩ ነገ ሲቀጥል በምድብ ለ የመጨረሻ ጨዋታዎች በተመሳሳይ  04:00 ላይ አዳማ ከ ወላይታ ድቻ (ወንጂ ሜዳ) እንዲሁም መከላከያ ከ ኢትዮጵየያ ንግድ ባንክ (አዳማ አበበ በቂላ ስታድየም) ይጫወታሉ፡፡

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *