የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሊግ የማጠቃልያ ውድድር በባቱ (ዝዋይ) ከተማ መከናወኑን ቀጥሏል፡፡ 3ኛ ቀኑን በያዘው ውድድርም ዛሬ በተደረጉ ጨዋታዎች ከፋ ቡና ፣ ሶሎዳ አደዋ እና ለገጣፎ ከተማ ድል ቀንቷቸዋል፡፡
08:00 ላይ በባቱ ሜዳ ከፋ ቡና ከ ወሊሶ ከተማ ባደረጉት የምድብ ሐ ጨዋታ ከፋ 2-1 አሸንፏል፡፡
የከፋ ቡናን የድል ጎሎች ምንተስኖት ታረቀኝ እና ተካልኝ መስፍን ሲያስቆጥሩ የወሊሶን ብቸኛ ጎል ሙሴ እንዳለ አስቆጥሯል፡፡
በተመሳሳይ 08:00 በሼር ሜዳ በተካሄደው የምድብ መ ጨዋታ ሶሎዳ አደዋ ሽሬ እንደስላሴን 2-1 አሸንፏል፡፡ የሶሎዳ አደዋን የድል ጎሎች ሽብሪል ጅራታ እና በፍቃዱ አለማየሁ ሲያስቆጥሩ የሽሬ እንደስላሴን ብቸኛ ጎል ያሲን አህምድ አስቆጥሯል፡፡
10:00 ላይ በባቱ ሜዳ ከምድብ ሐ በተደረገ ሌላ ጨዋታ ዞናቸውን በቻምፒዮንነት ያጠናቀቁት መተሀራ ስኳር እና አንበሪቾ 1-1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
ወንድወሰን ምህረቴ አንበሪቾን ቀዳሚ ሲያደርግ ዮርዳኖስ ዮሃንስ መተሃራ ስኳርን አቻ ያደረገች ግብ አስቆጥሯል፡፡
በተመሳሳይ 10:00 በሼር ሜዳ ላይ ከምድብ መ በተደረገ ጨዋታ ለገጣፎ ከተማ ዳባት ከተማን 2-1 አሸንፏል፡፡ የለገጣፎን የድል ጎሎች ብሩክ መርጊያ እና ልደቱ ለማ ሲያስቆጥሩ የዳባት ከተማን ብቸኛ ጎል ግዮን መላኩ አስቆጥሯል፡፡
ውድድሩ ነገ በእረፍት ምክንያት የማይደረግ ሲሆን ረቡዕ 2ኛ የምድብ ጨዋታዎች ይጀምራሉ፡፡
ረቡዕ 20/11/2008
04:00 ደሴ ከ አማራ ፖሊስ (ሼር ሜዳ)
04:00 ሚዛን አማን ከ አራዳ ክ/ ከተማ (ባቱ ሜዳ)
10:00 ወልቂጤ ከተማ ከ ሞጆ ከተማ (ሼር ሜዳ)
10:00 ዲላ ከተማ ከ ቡታጅራ ከተማ (ባቱ ሜዳ)
ካፋ ሁሌም 1ኛ ነው።።።።።።።።
kaffecho yegakisharecho!!! dill le kafa buna
እናመሰግናለን ሶከር ኢትዮጵያ፤ በተረፈ ‘አደዋ’ የሚለው ወደ ‘ዓድዋ’ ይስተካከል!
Kaffi bushoo kaffecho noone
ከፋ ሳይሆን…….ካፋ በሚል ይስተካከል
የለገጣፎን ግብ ያሥቆጠረው ብሩክ በርጌ ሣይሆን ብሩክ መርጊያ በሚል ይሥተካከል
ብራቦ ካፍ ቡና