ብሄራዊ ሊግ ፡ ከምድብ ሐ እና መ ወደ ሩብ ፍጻሜ ያለፉ ክለቦች ታውቀዋል

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር የምድብ ሐ እና መ የመጨረሻ የምድብ ጨዋታዎች ዛሬ ተካሂደዋል፡፡ ወደ ሩብ ፍጻሜ የተሸጋገሩ ክለቦችም ታውቀዋል፡፡

08:00 ላይ በሼር ሜዳ መተሃራ ስኳር  ካፋ ቡናን 2-1 በማሸነፍ ምድቡን በበላይነት አጠናቋል፡፡ የመተሃራ ስኳርን የድል ግቦች ዮርዳኖስ ዮሃንስ እና አረጋከኝ ለማ ሲያስቆጥር አሊ አብዲ የካፋ ቡናን ግብ አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ 08:00 ባቱ ሜዳ ላይ አምበሪቾ ወሊሶ ከተማን 5-2 ቢያሸንፍም ወደ ሩብ ፍጻሜ ለማለፍ በቂ አልሆነለትም፡፡

ቢንያም ጌታቸው 3 ግቦች አስቆጥሮ ሐት-ትሪክ ሲሰራ ደበላ ሮባ  እና ወንደሰን ምህረቴ  ቀሪዎቹን የሀምበሪቾ ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል፡፡  ሙሴ ባንቲ እና ዳንኤል በሃይሉ የወሊሶን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው፡፡

የምድብ ሐ ሰንጠረዥ

ክለብ – ተጫ (ልዩነት) ነጥብ

1 መተሃራ ስኳር    3   (+2)  7

2 ካፋ ቡና            3   (+2)  6

– – –  – – – – –

3 አምበሪቾ          3   (+1)   4

4 ወሊሶ ከተማ    3   (-5)   0

በምድብ መ 10:00 ላይ በሼር ሜዳ ሽረ እንዳስላሴ ዳባት ከተማን 3-1 በማሸነፍ ሩብ ፍፃሜውን ተቀላቅሏል፡፡

ከሊል ሃሰን ፣ ያሬድ ወ/ገብሬል እና  አቤል መብራቱ የሽረን ግብ ሲያስቆጥሩ ፊሊሞን ተኩ የዳባትን ብቸኛ ግብ አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ሰአት ባቱ ሜዳ ላይ ለገጣፎ ከተማ ሶሎዳ አድዋን 3-2 በማሸነፍ ምድቡን በበላይነት አጠናቋል፡፡ አስናቀ ተሽፊዬ እና  ሱሉቶ አለሙ (2) የለገጣፎን ግብ ሲያስቆጥሩ ጂብሩል ጁነይዲ እና በፍቃዱ አለማየሁ የሶሎዳን ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

የምድብ መ የደረጃ ሰንጠረዥ

ክለብ – ተጫ (ልዩነት) ነጥብ

ለገጣፎ ከተማ     3 (+2)    7

ሽረ እንዳስላሴ     3   (+1)   4

– – – – – – – –

ሶሎዳ አድዋ        3   (-1)    3

ዳባት  ከተማ       3   (-2)     3

* ውድ አንባቢዎቻችን በባቱ ከተማ የስልክ ኔትዎርክ በመቋረጡ ከሪፖርተራችን በፍጥነት መረጃዎችን መቀበል አልቻልንም፡፡ መረጃዎችን በዚህ ምክንያት ለማዘግየት መገደዳችንን ለማሳወቅ እንወዳለን

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *