የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ዛሬ ከወራቤ ከተማ ጋር ተስተካካይ ጨዋታውን ያደረገው ጅማ አባ ቡና ካለ ግብ አቻ ተለያይቶ ወደ ፕሪሚየር ሊግ መግባቱን ከወዲሁ አረጋግጧል፡፡
ከ25 ጨዋታዎች 61 ነጥቦችን የሰበሰበው ጅማ አባ ቡና 3ኛ ደረጃ ሊላይ ከሚገኘውና 26 ጨዋታ ካደረገው ወራቤ ከተማ በ13 ነጥቦች ርቆ በመቀመጡ ለከርሞ ወደ ሃገሪቱ ትልቅ ሊግ መሸጋገሩን አረጋግጧል፡፡
በ1947 በጅማ እርሻ ኮሌጅ አማካኝነት የተመሰረተው ጅማ አባ ቡና ከአመታት በፊት ከኢትዮጵያ እግርኳስ ካርታ ጠፍቶ በ2006 እንደገና በመመስረት በ3 አመታት ውስጥ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ አድጓል፡፡
ጅማ አባ ቡና ወደ ፕሪሚየር ሊግ ያደገ በታሪክ የመጀመርያው የጅማ ክለብ ሲሆን በፕሪሚየር ሊጉ የተሳተፈ 43ኛው ክለብ ለመሆን በቅቷል፡፡ በ1990ዎቹ መጀመርያ ጥቂት የሙገር ሲሚንቶ ጨዋታዎችን ከማስተናገድ ውጪ በፕሪሚየር ሊጉ ስም የሌላት ጅማ ከተማም በቀጣዩ አመት በሊጉ የሚወክላት ክለብ አግኝታለች፡፡
በጅማ አባቡና ወደ ፕሪሚየር ሊግ ማደግ ዙርያ ከክለቡ አሰልጣኝ እና ተጫዋቾች ጋር ያደረግነውን ቃለ ምልልስ ከቆይታ በኋላ ይዘን እንመለሳለን፡፡
Saba keetin boonii jimma
ኢትዮጵያ ቡና…. ሲዳማ ቡና …
ምናምን ቡና ስማችንን መልሱ
መቶዋልና ጅማ አባቡና ….
የቡና ምንጩ… የኳስ ንጉሱ
፣፣፣፣
፣፣፣፣
…………………………………….እኛ ሳንኖር የነገሳችሁ
ጊዮርጊስ …ደደቢት … መከላከያ… መጣንላችሁ!
We are Proud of your Work to promote to Ethiopian Premier League Competition….
Players I would like to Thank for your Unresereved Efferot during Your Time In higher League.Once Again CONGRATULATION!!
Jimma Ababuna Football Club Image and Proud of Jimma Town.
Long Live To Jimma Ababuna FC.
Congratulation, we deserve the premierlegue
አባ ቡናችን የጅማ ኩራት ኮራሁ በሁላችሁም
thanks all of u….im always with u….luv u much jimma ababuna…..
endetemegn nat agegnnat
mingize ababuuuuuuunaaaaaaaaaaaaaaa
is that true mesoud transfer to Gimma aba buna
Congratulations jimma abbunnaaaaaa ni monna ni mona ammas ni nimona
I will like to say congradulation to Jimma aba buna players,supporters and board of the club jimma aba buna players # golden boys
viva jimma ababuna