ጅማ አባ ቡና ከወዲሁ ኮከቦችን ማሰብሰብ ጀምሯል

በዛሬው እለት ወደ ፕሪሚየር ሊግ ማደጉን ያረጋገጠው ጅማ አባ ቡና ከወዲሁ የፕሪሚየር ሊግ ልምድ ያላቸው ተጫዋቾችን መሰብሰብ ጀምሯል፡፡

ጅማ አባ ቡና ከ5 ተጫዋቾች ጋር በቃል ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሱ የታወቀ ሲሆን በመጪዎቹ ቀናት በይፋ ከክለቡ ጋር ይፈራረማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የመከላከያ ውሉን የጨረሰው መሃመድ ናስር ወደ ትውልድ ከተማው የሚመልሰውን ዝውውር ሲያደርግ ከመከላከያ ጋር በውል ማራዘም ላይ ከስምምነት መድረስ ያልቻለው  የብሄራዊ ቡድኑ ግብ ጠባቂ ጀማል ጣሰውም አጥቂውን ተከትሎ ወደ ጅማ አምርቷል፡፡

PicsArt_1468657260802

በውድድር ዘመኑ ድንቅ አቋም ያሳየው የወላይታ ድቻው የአጥቂ አማካይ በድሉ መርዕድ ሌላው ለጅማ አባ ቡና ለመፈረም የተስማማ ተጫዋች ሲሆን የክለብ አጋሩ ኃይለየሱስ ብርሃኑም ጅማ ደጃፍ ደርሷል፡፡ ኃይለየሱስ በተከላካይ እና አማካይነት መጫወት የሚችል ተጫዋች ነው፡፡

PicsArt_1470077428054

አስከ ውድድር ዘመኑ መጨረሻ በሚቆይ ውል ኤሌክትሪክን ያገለገለው ፍጹም ገብረማርያም ሌላው ለጅማ አባ ቡና ለመፈረም የተስማማ ተጫዋች እንደሆነ ከክለቡ ያገኘነው መረጃ ቢያመለክትም በዩናይትድ ስቴትስ የእረፍት ጊዜውን እያሳለፈ የሚገኘው የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ ኮከብ ከክለቡ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንዳላደረገ ለሶከር ኢትዮጵያ ገልጿል፡፡ በቀጣዩ ሳምንት ወደ ሀገር ቤት ሲመለስ ቀጣይ ማረፊያውን እንደሚወስንን ጨምሮ ተናግሯል፡፡

PicsArt_1470077267391

ለአባ ቡና ለመፈረም ከስምምነት ከደረሱት ተጫዋቾች መካከል መስኡድ መሃመድ አንዱ ነው፡፡ መስኡድ ከቡና ጋር ያለው ኮንትራት እስካሁን ያልታደሰ ሲሆን በክለቡ ያለውን ቆይታ አጠራጣሪ ሆኗል፡፡

ጅማ አባ ቡና በዝውውር መስኮቱ ንቁ ተሳታፊ መሆን የቻለ ሲሆን በቀጣዩ የውድድር ዘመን ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ ለመቅረብ ስራዎች እየሰራ እንደሆነ ከክለቡ አካባቢ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *