የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ጥሎ ማለፍ በትላንትናው እለት ፍጻሜውን ሲያገኝ ሀዋሳ ከተማ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል፡፡
በቦዲቲ ስታድየም በወላይታ ድቻ እና ሀዋሳ ከተማ መካከል በተደረገው የፍጻሜ ጨዋታ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ 3-3 ተጠናቋል፡፡
ልጅአለም መላኩ ፣ ሲሳይ ማሜ እና ክብሩ በለጠ ለወላይታ ድቻ ሲያስቆጥሩ ያሬድ መሃመድ (ፍቅም) ፣ ገብረመስቀል ዱባ እና እስራኤል እሸቱ ለሀዋሳ ከተማ አስቆጥረዋል፡፡
አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠው የመለያ ምት ሀዋሳ ከተማ 4-2 በማሸነፍ የውድድር ዘመኑን በሁለትዮሽ ዋንጫ ደምድሟል፡፡ የሀዋሳው ግብ ጠባቂ አላዛር መርኔ 2 የመለያ ምቶችን በማዳን ለቡድኑ አሸናፊነት ትልቁን ሚና ተወጥቷል፡፡
ሀዋሳ ከተማ በ17 አመት በታች ፕሪሚየር ሊግ የዞኑን እና የማጠቃለያ ውድድሩን በቻምፒዮንነት ማጠናቀቁ የሚታወስ ነው፡፡