ድሬዳዋ ከተማ እና ወላይታ ድቻ ከብሄራዊ ሊጉ ተጫዋቾች አስፈርመዋል

ወላይታ ድቻ እና ድሬዳዋ ከተማ በባቱ እየተካሄደ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሊግ የማጠቃለያ ውድድር ተጫዋቾችን አስፈርመዋል፡፡

ውድድሩን ሲከታተሉ የቆዩት የወላይታ ድቻው አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ድንቅ ብቃታቸውን ሲያሳዩ የነበሩት የካፋ ቡናው ፉአድ ተማም እና የመተሃራ ስኳሩ ዮርዳኖስ ዮሐንስን ለሶስት አመታት አስፈርመዋል፡፡

PicsArt_1470662609703
ዮርዳኖስ ዮሃንስ

የበዛብህ መለዮን ኮንትራት ያደሰው ድቻ ተጨማሪ ተጫዋቾችን ለማስፈረም በድርድር ላይ የሚገኝ ሲሆን በቅርቡ ከከፍተኛ ሊግ ተጫዋቾች ሊያስፈርም እንደሚችል ታውቋል፡፡

PicsArt_1470662656027
ዘሪሁን አሸንቦ

እንደ ወላይታ ድቻ ሁሉ ድሬዳዋ ከተማም አይኑን በመተሃራ እና ካፋ ቡና ላይ በመጣል ሁለት ተጫዋቾችን አስፈርሟል፡፡

የመተሃራ ስኳሩ ተከላካይ ዘሪሁን አሸንቦ እና የካፋ ቡናው አጥቂ ምንተስኖት ታረቀኝ ለአሰልጣኝ ዘላለም ሽፈራው ቡድን ለ2 አመት የፈረሙ ተጫዋቾች ናቸው፡፡

ምንተስኖት ታረቀኝ

ድሬዳዋ ከተማ በርካታ ተጫዋቾችን በማስፈረም ላይ የሚገኝ ሲሆን ከደቡብ ፖሊስ የመስመር አማካዩ ምስጋናውን ማስፈረም ችሏል፡፡ ምስጋናው ከዘላለም ኢሳያስ እና ሚካኤል ለማ በመቀጠል ለድሬዳዋ የፈረመ 3ኛው የደቡብ ፖሊስ ተጫዋች ሆኗል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *