የኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና በቢሸፍቱ አውቶሞቲቭ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

ወደ ብሄራዊ ሊግ የሚያድጉ ክለቦችን ለመለየት በአርባምንጭ ከተማ አስተናጋጅነት ከሐምሌ 21 – ነሐሴ 8 ሲካሄድ የቆየው የኢትዮዽያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ዛሬ ፍጻሜውን አግኝቷል፡፡

በመዝጊያ ስነስርአቱም የጋሞ ጎፋ ዞን ም/ስራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ አባተ የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ቾል ቤል ፣ የተጂ ከተማ ከንቲባ ታምሩ ካህሳይ የቢሸፍት አውቶሞቲቭ ም/ ስራ አስኪያጅ ኮ/ል ሄዶ ሻኮ ተገኝተዋል፡፡

03:00 ላይ በተደረገው የደረጃ ጨዋታ ሀዲያ ሊሞ ከ ጨንቻ ከተማ በመደበኛው ክፍለ ጊዜ ያለግብ አገባደው በተሰጡት የመለያ ምቶች ሀዲያ ሊሞ 5 – 3 በማሸነፍ ሦስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡

09:00 ላይ በተካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ ቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ተጂ ከተማን ከፍፁም የጨዋታ ብልጫ ጋር 3-0 በማሸነፍ የውድድሩ ቻምፒዮን ሆኗል፡፡

ከጨዋታው ፍፃሜ በኋላ የሽልማት መርሐ ግብር ቀጥሏል፡፡

የኮከቦች ሽልማት

PicsArt_1471192475463

ኮከብ ዋና ዳኛ

ብርሃኑ መኩሪያ – 3000 ብር እና ዋንጫ

ኮከብ ረዳት ዳኛ

ለአለም ዋሲሁን – 3000 ብር እና ዋንጫ

PicsArt_1471192565715

ኮከብ ተጨዋች

አስፕሬ መሀመድ (ሀዲያ ሊሞ) – 5000 ብር እና ዋንጫ

ኮከብ ግብ ጠባቂ

ንጉሴ ሙልጌታ (ጨንቻ ከተማ) – 5000 ብር እና ዋንጫ

ኮከብ ጎል አስቆጣሪ

ኢሳያስ ብርሃኔ (ቢሸፍቱ አ.) እና ማቲዮስ ኤልያስ (ጨንቻ ከተማ) በ5 ግቦች – ዋንጫ እና 2500 ብር ለእያንዳንዳቸው

PicsArt_1471192394391

ኮከብ አሰልጣኝ

ግዛው ልኬ (ቢሸፍቱ) – 5000 ብር እና ዋንጫ

የስፖርታዊ ጨዋነት ዋንጫ – ቢሸፍቱ አ.

PicsArt_1471192689349

የደረጃ ሽልማቶች

1ኛ. ቢሸፍቱ አውቶሞቲቭ – 30,000 ብር ፣ የወርቅ ሜዳልያ እና ዋንጫ

2ኛ. ተጂ ከተማ – 25,000 ብር እና የብር ሜዳልያ

3ኛ. ሀዲያ ሊሞ – 15,000 ብር እና የነሐስ ሜዳልያ

በ8 ምድብ ተከፍሎ በ35 ክለቦች መካከል ሲካሄድ ከሰነበተው የኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና 8 ክለቦች ወደ 2009 ብሄራዊ ሊግ ማደጋቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ወደ ብሄራዊ ሊግ ያለፉ ክለቦች

1 ወለንጪቲ

2 ቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ  

3 ለገጣፎ ከተማ ቢ 

4 ጨንቻ ከተማ 

5 ራያ ከተማ 

6 ተጂ ከተማ 

7 ሀዲያ ሊሞ 

8 ገላን ከተማ


 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *