የኢትዮጵያ ከ17 አመት ብሄራዊ ቡድን ለመልሱ ጨዋታ በድሬዳዋ ዝግጅቱን ቀጥሏል

የኢትዮዽያ ከ17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን በአፍሪካ ከ17 አመት ዋንጫ ማጣርያ ከግብጽ ጋር የመልስ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

በአሰልጣኝ አጥናፉ የሚመራው ታዳጊ ብሄራዊ ቡድን ከካይሮ በ3-1 ድል ከተመለሰ በኋላ ወደ ድሬደዋ በማቅናት ለመልሱ ጨዋታ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡

በራስ ሆቴል በመክተም ልምምዱን ከጀመረ  8ኛ ቀኑን የያዘው ታዳጊ ቡድኑ በጥሩ ፍላጎት እና መነሳሳት ልምምዳቸውን ሲሰሩ ለማየት ችለናል፡፡ ማጥቃትን መሰረት ያደረገ አጨዋወት ፣  ለሁለት ተከፍሎ በግማሽ ሜዳ መጫወት እና የቆሙ ኳሶችን አክርሮ የመምታት  ልምምዶች የዛሬው መርሃ ግብራቸው አካል ነበር፡፡

በድሬዳዋ ያለውን ከፍተኛ ሙቀት መላመድ ተስኗቸው የተወሰኑ ተጨዋቾች የመንሰር ችግር አጋጥሟቸው በህክምና ባለሙያ ድጋፍ ሲደረግላቸውም አይተናል፡፡

PicsArt_1471533199346

ተጋጣሚው የግብፅ ብሔራዊ ቡድን 35 የልኡካን ቡድን በመያዝ ነገ ጠዋት አአ በመግባት ወድያው ወደ ድሬዳዋ እንደሚያቀና የሚጠበቅ ሲሆን ሳምራን ሆቴል ማረፊያው እንደሚሆን ለማወቅ ችለናል፡፡ ጨዋታውን የሚመሩት አራቱም ዳኞቹ ሱዳናውያን ሲሆኑ ኮሚሽነሩ ደግሞ ከኬንያ ነው፡፡

PicsArt_1471533261580

የኢትዮጵያ እና የግብጽ ከ17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድኖች የመልስ ጨዋታ በመጪው እሁድ ድሬዳዋ ስታድየም ላይ ይደረጋል፡፡ የድሬደዋ ስታድየም የተመልካች ቁጥር አቅሙን ለማሳደግና በተለምዶ በካታንጋ እና ጥላ ፎቁ ግራና ቀኝ  የስታድየሙ ክፍል ተጨማሪ መቀመጫዎችን ለመስራት ግንባታው እየተፋጠነ መሆኑን ለማየት ችለናል፡፡

PicsArt_1471534318145

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *