የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን በአፍሪካ ከ17 አመት በታች ዋንጫ ማጣርያ ከማሊ ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ ዝግጅቱን ዛሬ ጀምሯል፡፡
በአዲስ አበባ ስታድየም የመሮጫ መም ላይ በነበረው ልምምድ ለተጫዋቾቹ የፍጥነትና የአካል ብቃት ሙከራ ተደርጎላቸዋል፡፡
አሰልጣኝ አጥናፉ አባተ በሀዋሳ እየተካሄደ ከሚገኘው የክልል ፕሮጀክቶች የምዘና ውድድር እና ወላይታ ድቻ ተጫዋቾችን በመመልመል የተመለሱ ሲሆን ተጫዋቾቹ የMRI ምርመራ አድርገው ተገቢ ከሆኑ ከቡድኑ ጋር ይቀላቀላሉ ተብሏል፡፡
በረከት መንገሻው ፣ አስቻለው ግርማ እና ፉአድ ተማም ከወላይታ ድቻ የተመረጡ ሲሆን ፉአድ ዘንድሮ በካፋ ቡና ድንቅ አቋሙን አሳይቶ ወደ ድቻ የተዘዋወረ ተጫዋች ነው፡፡
ፍቃደ ስላሴ ደሳለኝ ፣ ፍፁም ተስፋዬ ፣ በረከት ግርማ ፣ ማቲዮስ መርኪን እና ይፍታለም ታፈሰ ደግሞ ከፕሮጀክቶቹ የምዘና ውድድር የተመረጡ ተጫዋቾች ናቸው፡፡