​ብሄራዊ ቡድኑ ዝግጅቱን ሲቀጥል ዋሊድ አታ ቡድኑን ተቀላቅሏል

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከሲሸልስ ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ ዝግጅቱን ቀጥሏል፡፡ ዋሊድ አታም ብሄራዊ ቡድኑን ትላንት ተቀላቅሏል፡፡

ዛሬ 10:00 ላይ በነበረው ልምምድ ላይ በሲሸልሱ ጨዋታ ላይ ቋሚ ተሰላፊ የሚሆኑ ተጫዋቾችን ፍንጭ በሚሰጥ መልኩ ለሁለት ተከፍለው ተጫውተዋል፡፡ በዛሬው ልምምድ ላይ ትላንት ቡድኑን የተቀላቀለው ዋሊድ የተገኘ ሲሆን አቤል ማሞ እና እንዳለ ከበደ በልምምዱ ላይ አልተሳተፉም፡፡ አህመድ ረሺድ መጠነኛ ጉዳት አጋጥሞት ልምምዱን አቋርጦ የወጣ ሲሆን ሌሎቹ ተጨዋቾች በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛሉ፡፡

PicsArt_1472749449322

የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን 19 የቡድን አባላትን ይዞ ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ የሚገባ ሲሆን የተቀረው የልኡካን ቡድን ነገ አመሻሽ ላይ የሚገባ መሆኑ ለጨዋታው የሰጠው ግምት አነስተኛ መሆኑን ያሳያል፡፡

ጨዋታው ቅዳሜ በአዲሱ የሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታድየም የሚካሄድ ሲሆን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ከጣልያኑ ኤሪያ ጋር በገባው ውል መሰረት ዋልያዎቹ ለመጀመርያ ጊዜ የኤሪያ ምርቶችን ለብሰው ወደ ሜዳ ይገባሉ፡፡

PicsArt_1472751886966

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *