ሲሸልስ የመጀመርያ ፣ ኢትዮጵያ የመጨረሻ ልምምዳቸውን ሰርተዋል

የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን ዛሬ የመጀመርያ ልምምዱን በሀዋሳ ሰርቷል፡፡ ትላንት ማምሻውን አአ ገብቶ ዛሬ ሀዋሳ የመጣው የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን 11:00 ላይ ቀለል ያሉ እና የቆሙ ኳሶች ልምምድ በሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስቴዲዮም ሰርቷል፡፡

የሲሸልስ ብሄራዊ ቡድን 21 የልኢ።ካን ቡድን አባላት ይዞ ኢትዮጵያ የመጣ ሲሆን ከነዚህ መካከል 19ኙተጫዋቾች ናቸው፡፡ ተጨማሪ አምስት አባላት ደግሞ ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ የሚገቡ ይሆናል፡፡

PicsArt_1472833605901

የኢትዮዽያ ብሄራዊ ቡድን በበኩሉ ዛሬ ረፋድ ላይ የመጨረሻ ልምምዱን አከናውኗል፡፡ በዛሬው ልምምድ የቆሙ ኳሶችን የመምታት ልምምድ የሰሩ ሲሆን አሰልጣኝ ገብረመድህን ለነገው ጨዋታ የሚጠቀሙባቸውን 18 ተጫዋቾች ዛሬ ያሳውቃሉ፡፡  አቤል ማሞ ፣ እንዳለ ከበደ እና አህመድ ረሺድ በጉዳት ከ18ቱ ውጪ መሆናቸው የተረጋገጡ ተጫዋቾች ናቸው፡፡

PicsArt_1472833932441

ጨዋታውን የሚመሩት ዳኞች

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *