የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀመርበት ቀን ተራዘመ

የ2009 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀመርበት ቀን ለውጥ እንደተደረገበት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሸን አስታውቋል፡፡

ሊጉ ይጀመራል ተብሎ የወጣለት ቀን መስከረም 29/2009 ሲሆን አዲስ በወጣው ቀን መሰረት ጥቅምት 20 ቀን 2008 ይጀመራል፡፡ መስከረም 5 ሊወጣ የነበረው የእጣ ማውጣት ስነስርአትም ለጥቅምት 12 ተዛወሯል፡፡

ፌዴሬሽኑ ለቀኑ መራዘም በምክንያትያትነት ያስቀመጠው ወደ ፕሪሚየር ሊግ ያደጉት ፋሲል ከተማ ፣ ጅማ አባ ቡና ፣ አአ ከተማ እና ወልድያ የእረፍት እና የዝግጅት ጊዜ እጥረት እንደሚያጋጥማቸው በመግለፅ እንዲራዘም ጥያቄ በማቅረባቸው እንዲሁም ሜዳዎች ለጨዋታዎች ዝግጁ ባለመሆናቸው እንደሆነ ታውቋል፡፡



[socialpoll id=”2385802″]

[socialpoll id=”2385807″]

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *