ፋሲል ከተማ ያሬድ ባየህን ሲያስፈርም የአብዱልራህማንን ኮንትራት አድሷል

 የዝውውር ዜና | 03-01-2009 

ፋሲል ከተማ የዳሽኑ ተከላካይ ያሬድ ባየህን የግሉ ሲያደርግ የኮከቡ አብዱልራህማን ሙባረክን ኮንትራት አድሷል፡፡

አማራ ውሃ ስራን ለቆ ባለፈው ክረምት ዳሽንን የተቀላቀለው ያሬድ በአጭር ጊዜ በሊጉ ከሚገኙ ምርጥ ተከላካዮች አንዱ መሆን የቻለው ያሬድ ወደ ደደቢት ለማምራት ተቃርቦ የነበረ ቢሆንም ሌላኛው የከተማው ቡድን ፋሲልን መቀላቀል ምርጫው አድርጓል፡፡

ፋሲል ከተማ በዚህ ክረምት ከዳሽን ቢራ ያስፈረማቸው ተጫዋቾች 3 ደርሰዋል፡፡ አጥቂው ኤርሚያስ ኃይሉ እና የመስመር ተከላካዩ አምሳሉ ጥላሁን አሁን ደግሞ ያሬድ ባየህ ዳሽንን ለቀው ፋሲልን ተቀላቅለዋል፡፡

ፋሲል ከተማ በዘንድሮ የውድድር አመት ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ ለመቅረብ የክለቡን ወሳኝ ተጨዋቾችን ውል በማደስ ላይ ይገኛል፡፡  ከነዚህም መካከል የአመቱ የከፍተኛ ሊግ ኮከብ ተጨዋች ሆኖ ያጠናቀቀው አብዱልራህማን ሙባረክ ውሉን ያደሰ ተጫዋች ሆኗል፡፡

picsart_1469120719731-615x360

ከክለቡ ጋር በተያያዘ የዝውውር ዜና አምስት የውጭ ዜጋ ተጨዋቾችን በማምጣት የሙከራ ጊዜ ሰጥቶ ለማየት ለክለቦችና ተጨዋቾች ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን በቅርብ ቀናት መጥተው የተሳካ የሙከራ ጊዜ የሚያሳልፉትን ለማስቀረት እንቅስቃሴ መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የከፍተኛ ሊጉ የምድብ እና አጠቃላይ አሸናፊ ለሆነው ፋሲል ከተማ የክልሉ መንግስት የገንዘብና ለተጨዋቾች ማመላለሻ ዘመናዊ አውቶቢስ በስጦታ ሲያበረክት በጎንደር ከተማ ከፍተኛ የሆነ አቀባበል ሊደረግለት እንደታሰበም ታውቋል፡፡

ፋሲል ከተማ የአዲሱ የውድድር ዘመን ዝግጅቱን ከመስከረም 6 ቀን 2009 አንስቶ በቢሸፍቱ ከተማ ይጀምራል፡፡


[socialpoll id=”2385802″]

[socialpoll id=”2385807″]


picsart_1473774112526

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *