ሴካፋ ሴቶች ዋንጫ : ኢትዮጵያ ከ ኬንያ የውድድሩን ታላቅ ጨዋታ ያደርጋሉ

 የሴቶች እግርኳስ | 07-01-2009 

የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ ተሸጋግሯል፡፡ ነገ የሚደረጉት ሁለት የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች ወደ ፍጻሜ የሚያልፉትን ሃገራትን ይለያሉ፡፡

በእጣ የምድቧን ሁለተኛ ደረጃ ይዛ ያጠናቀቀችው ኢትዮጵያ የውድድሩ አሸናፊነት ቅድሚያ ግምት የተሰጣት ኬንያን ነገ 07:30 ላይ ትገጥማለች፡፡

ኬንያ ካሜሩን በምታስተናግደው የአፍሪካ ሴቶች ዋንጫ ተሳታፊ መሆኗን ያረጋገጠች ብቸኛ የምስራቅ አፍሪካ ሀገር ስትሆን ያለፈችውም ኢትዮጵያን ጥላ ያለፈችው አልጄርያን አሸንፋ ነበር፡፡ ኬንያ በሴካፋ ባደረገቻቸው 3 ጨዋታዎች 19 ግቦችን ተጋጣሚዋ ላይ ስታስቆጥር ምንም ግብ ሳታስተናግድ በአስፈሪ ወቅታዊ አቋም ላይ ትገኛለች፡፡

በምድብ ለ ሩዋንዳን 3-2 አሸንፋ ከታንዛኒያ አቻ የተለያችው ኢትዮጵያ ከኬንያ በመቀጠል ለዋንጫው ከፍተኛ ግምት ያገኘች ሃገር እንደመሆኗ የነገው ጨዋታ ከፍጻሜ በፊት የሚደረግ ሌላ የፍጻሜ ጨዋታ እንደማለት ነው፡፡  የኢትየጵያ አሰልጣኝ መሰረት ማኒም ጨዋታው ጠንካራ እንደሚሆን ግምታቸውን ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡ ” ጨዋታው ጠንካራ ፉክክር እና ጥሩ ጨዋታ የሚታይበት ይሆናል ” ብለዋል፡፡

picsart_1474143021799

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት በ2012 አዲስ አበባ ላይ በወዳጅነት ጨዋታ ሲሆን ሉሲዎቹ 5-0 ማሸነፍ ችለው ነበር፡፡ በሴካፋው ውድድር አድናቆት የተቸራት ሽታዬ ሲሳይ በወቅቱ 3 ግቦች አስቆጥራ ሐት-ትሪክ መስራቷ የሚታወስ ሲሆን ኬንያ በ20 አመታት ውስጥ የደረሰባት ከፍተኛው ሽንፈት ሆኖ ተመዝግቦ ነበር፡፡

አሰልጣኝ መሰረት ቡድናቸው አሁንም ኬንያን ለማሸነፍ እንደተዘጋጁ ተናግረዋል፡፡ ” ያለንን አቅም ሁሉ ተጠቅመን ውጤታማ ለመሆን በሚገባ ተዘጋጅተናል፡፡ ጥሩ ነገር ይኖራል ብዬ አስባለው”

picsart_1474142989141

የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች

07:30 ኬንያ ከ ኢትዮጵያ

09:30 ዩጋንዳ ከ ታንዛንያ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *