ዋልያዎቹ መቼ ዝግጅት እንደሚጀምሩ አልታወቀም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለወትሮው ለትልልቅ ውድድሮች ቢያንስ አንድ ወር ዝግጀት የማድረግ ልማድ ቢኖረውም በ2014 መጀመርያ በሀገር ውስጥ ሊግ ውስጥ በሚጫወቱ ተጫዋቾች ብቻ በሚዋቀር ስብስብ ለሚደረገው ውድድር (ቻን) እስካሁን ዝግጅት አልጀመረም፡፡
ውድድሩ ሊጀመር የ23 ቀናት እድሜ የቀሩት ቢሆንም ኢትዮጵያ እስካሁን ተጫዋቾቿን አላሳወቀችም (በምድባችን የምትገኘው ጋና ከወዲሁ 23 ተጫዋቿን አሳውቃለች)፡፡ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በመጪው ሳምንት ሰኞ ዝግጅት ለመጀመር ጥያቄ ቢያቀርቡም የሊጉ ውድድር እንዳይቋረጥ በሚል በፌዴሬሽኑ ውድቅ ተደርጎባቸዋል፡፡
ኢትዮጵያ በቻን ምድብ ሦስት ከኮንጎ ሪፐብሊክ (ብራዛቪል)፣ ሊቢያ እና ጋና ጋር መደልደሏ ይታወሳል፡፡
© ሶከር ኢትዮጵያ
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...
Average Rating