የሊጉ ሁለት ተስተካካይ ጨዋታዎች የካቲት ወር ላይ ይደረጋሉ

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2ኛ ሳምንት ሊካሄዱ የነበሩትና በተለያዩ ምክንያቶች  ሳይካሄዱ የቀሩት ጨዋታዎች መቼ እንደሚካሄዱ ሶከር ኢትዮጵያ ከፌዴሬሽኑ አረጋግጣለች፡፡

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ሀዋሳ ከተማ በአዲስ አበባ ስታድየም እንዲሁም ፋሲል ከተማ ከ ወላይታ ድቻ በአፄ ፋሲለደስ ስታድየም የሚያዳድጉት ጨዋተ የፕሪሚየር ሊጉ 1ኛ ዙር ከተጠናቀቀ በኋላ ባሉት ቀናት ይካሄዳል፡፡ የፕሪሚየር ሊጉ 1ኛ ዙር ጥር 28 የሚጠናቀቅ በመሆኑ ሁለቱ ጨዋታዎች የካቲት ወር መጀመሪያ የሚካሄዱ ይሆናል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *