ወላይታ ድቻ የገቢ ማሰባሰብያ ሩጫ ውድድር ያካሂዳል
የወላይታ ድቻ እግር ኳስ ክለብ ራሱን በገቢ ለማጠናከር በማሰብ የሩጫ ውድድር አዘጋጅቷል፡፡
በ2006 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን ከተቀላቀለ ወዲህ በአነስተኛ ወጪ በሊጉ ተፎካካሪ መሆን የቻለው ወላይታ ድቻ ክለቡን ለማጠናከር የፊታችን ታህሳስ 15 በወላይታ ሶዶ ከተማ 15ሺህዝብ የሚሳተፍበት የአምስት ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ያከናውናል፡፡ በርካታ ደጋፊ ያለው ድቻ ውድድሩን ያዘጋጀበት አላማ የክለቡን ህዝባዊነት ከድጋፍ ባለፈ ወደ ገንዘብ ለመለወጥ በማለም መሆኑን ለሶከር ኢትዮጵያ አስታውቋል፡፡
ወላይታ ድቻን በገንዘብ እንዲሁም በቁሳቁስ 15 ሺህ አርሶአደሮች ፣ 20ሺህ የመንግሥት ሰራተኞች ፣ 12 ባለሀብቶች እንዲሁም በአዲስ አበባ ከሚኖሩ የክለቡ ወዳጆች ድጋፍ እንደሚደረግለትም ተገልጿል፡፡ ክለቡ ባሳለፍነው መስከረም ከሲዳማ ቡና እና ኢትዮጰያ ቡና ጋር የወዳጅነት ጨወታዎችን በማድረግ ለወላጅ አልባ ህጻናት እርዳታ ማዋሉ ይታወሳል፡፡
ክለቦች ለገቢ ማሰባሰብያ የሩጫ ውድድር ሲያደርጉ ይህ የመጀመርያ ጊዜ አይደለም፡፡ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ ቡና እና ሀዋሳ ከተማ ማዘጋጀታቸውም ይታወሳል፡፡
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...
Average Rating