በፕሪሚየር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደደቢትን አሸንፎ 1ኛውን ዙር መሪነት ጨረሰ
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ትላንት ምሽት አንድ ተስተካካይ ጨዋታ አስተናግዶ መሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ደደቢትን ረቷል፡፡ ጨዋታው በሁለት ታላላቅ ቡድኖች መካከል የተካሄደ በመሆኑ በበርካቶች በጉጉት እንዲጠበቅ ቢያደርግም ከጨዋታው መጀመር በፊት መጣል የጀመረው ከባድ ዝናብ ጨዋታውን እንዳያስተጓጉለው ተፈርቶ ነበር፡፡
አሰልጣኝ ማርት ኑይ ደጉ ደበበን የተከላካይ አማካይነት ሚና ሲሰጡት አዳና ግርማን ወደ ፊት አስጠግተው አጫውተውታል፡፡ ካለ ዳዊት ፍቃዱ እና አዳሙ መሃመድ ወደ ሜዳ የገቡት አሰልጣኝ ንጉሴ ደስታ ደግሞ በሁለቱ ምትክ ዘነበ ከበደ እና አሸናፊ አደምን በቋሚ አሰላለፉ አካተዋል፡፡
በመጀመርያው አጋማሽ ቅዱስ ጊዮርጊስ በተደጋጋሚ ወደ ግብ መድረስ ሲችል ኡመድ ኡኩሪ እና ሳሙኤል ሳኑሚ በተደጋጋሚ የታሪኩ ጌትነትን ግብ ለመድፈር ጥረት አድርገዋል፡፡ በተለይም ኡመድ ኡኩሪ ከቅጣት ምት አክርሮ የመታት ኳስ በጥሩ የግብ እድልነት የምትጠቀስ ነበረች፡፡ በ26ኛው ደቂቃ ሳሙኤል ሳኑሚ ግብ ቢያስቆጥርም ረዳት ዳኛው በአወዛጋቢ ሁኔታ ከጨዋታ ውጪ ምልክት አሳይተዋል፡፡ በዚህ 45 ደቂቃ ደደቢት በመከላከሉ የተሸለ የነበረ ቢሆንም ወደ ግብ መድረስ የቻሉባቸው አጋጣሚዎች ጥቂት ነበሩ፡፡
በሁለተኛው አጋማሽ ተመጣጣኝ የነበረው ፉክክር ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ አመዝኖ በ63ኛው ደቂቃ አዳነ ግርማ ከኡመድ ኡኩሪ የተሸገረለትን ኳስ ተጠቅሞ ቅዱስ ጊዮርጊስን መሪ አድርጓል፡፡ ለመጀመርያው ግብ መገኘት አስተዋፅኦ ያደረገው ኡመድ ኡኩሪ የቅዱስ ጊዮርጊስን መሪነት ወደ ሁለት ከፍ ያደረጋትን ግብ በ78ኛው ደቂቃ በጥሩ አጨራረስ አስቆጥሯል፡፡
ደደቢቶች ወደ ጨዋታው ለመመለስ ያደረጉት ጥረት እምብዛም ፍሬያማ አልነበረም፡፡ የቀድሞው የቅዱስ ጊዮርጊስ የመስመር አማካይ መስፍን ኪዳኔ ከተጠባባቂ ወንበር ተነስቶ በ86ኛው ደቂቃ ግብ አስኪያስቆጥር ድረስም ይህ ነው የሚባል የግብ እድል መፍጠር ሳይችሉ ጨዋታው በቅዱስ ጊዮርጊስ 2-1 አሸናፊነት ተጠናቋል፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከድሉ በኋላ በ13 ጨዋታዎች በ1ዱ ብቻ ተሸንፎ 12 አሸንፎ 29 ግቦች ከመረብ አሳርፎ 6 ግቦች ብቻ ተቆጥረውበት በ36 ነጥቦች የመጀመርያውን ዙር በመሪነት አጠናቋል፡፡ አሰልጣኝ ማርት ኑይም በድል የቅዱስ ጊዮርጊስ ቆይታቸውን አሳርገዋል፡፡
ደደቢት በበኩሉ 2 ቀሪ ጨዋዎች በእጁ ያሉት ሲሆን መጋቢት 25 ከሀዋሳ ከነማ መጋት 29 ደግሞ ከወላይታ ድቻ ጋር ከባድ ፍልሚያ ይጠብቀዋል፡፡
ከደደቢት በተጨማሪ ኢትዮጵያ ቡና ከሐረር ቢራ ረቡእ መጋቢት 24 የሚያደርገው ጨዋታ ሌላው የ1ኛው ዙር ተስተካካይ መርሃ ግብር ነው፡፡
{jcomments on}
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...
Average Rating