ዳሽን ቢራ ሳምሶን አየለን አሰናበተ
ዳሽን ቢራ የክለቡ ዋና አሰልጣኝ የሆነው ሳምሶን አየለን ከኃላፊነት ማንሳቱን አስታውቋል፡፡ ዛሬ ጠዋት በተደረገው የቦርድ ስብሰባ አሰልጣኙ የሚጠበቅባቸውን ውጤት ማስመዝገብ ባለመቻላቸው ከኃላፊነታቸው ለማንሳት ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡
በክረምቱ የዝግጅት ወቅት ዳሽን ቢራን በከፍተኛ የፊርማ ክፍያ የተረከቡት የቀድሞው የሐረር ሲቲ አሰልጣኝ በከፍተኛ የፊርማ ክፍያ የተገዙ ተጫዋቾችን ያሰባሰበ ከፍተኛ ልምድ ያለው ስብስብ ቢይዙም ቡድኑን በወራጅ ቀጠና እንዲገኝ ማድረጋቸው ከደጋፊው ከፍተኛ ተቃውሞ እንዲነሳባቸው አድርጓል ተብሏል፡፡
የዳሽን ዋና አሰልጣኝነት ቦታን ምክትሉ ካሊድ መሃመድ የሚይዙት ሲሆን አሰልጣኙ ባለፈው የውድድር ዘመን አሰልጣኝ መኮንን ከተሰናበቱ በኋላ በጊዜያዊ አሰልጣኝነት የውድድር ዘመኑን ማጠናቀቃቸው ይታወሳል፡፡
ፎቶ – Dashen Beer FC.
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...
Average Rating