ደደቢት ከ ኢትዮጵያ ቡና | ቀጥታ የፅሁፍ ስርጭት

FT   ደደቢት   0-0   ኢትዮጵያ ቡና  

ተጠናቀቀ!!!

ጨዋታው ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል፡፡

90+1 ከሳምሶን ጥላሁን የደረሰውን ኳስ በመጠቀም ጌታነህ ከበደ ከቡናዎች ሳጥን ውስጥ መሬት ለመሬት ቢሞክርም ኳስ በጎን ወጥታለች ።

90′ ጭማሪ ደቂቃ 3!

89′ ደደቢቶች ወደ ቡናዎች የሜዳ ክፍል በመግባት ተጭነው ለመጫወት እየሞከሩ ይገኛሉ ።
86′ ጌታነህ ከበደ በግል ጥረቱ በግራ መስመር በቡና ተከላካዮች መሀል ይዞ የገባውን ኳስ ለሽመክት ወደ ውስጥ ለማሳለፍ ቢሞክርም ኳሷ ሽመክት ጋር ከመድረሷ በፊት ሀሪሰን ይዟታል ።
83 ‘ቢጫ ካርድ ደደቢት ! 

ከደር ኩኒባሊ ጋቶችን መሀል ሜዳ ላይ ጎትቶ በማስቀረቱ የጨዋታውን የመጀመሪያ የማስጠንቀቂያ ካርድ ተመልክቷል ።

83’የተጨዋች ለውጥ ኢትዮጵያ ቡና 

ያቡን ዊልያም በእያሱ ታምሩ ተተክቷል

81′ የደደቢቶች ጥቃት በኢትዮጵያ ቡና የሜዳ ክፍል ላይ ጎል ለማስቆጠር የሚረዳ ቦታ ላይ ከመድረሱ በፊት በተደጋጋሚ የተቅቋረጠ ይገኛል ።

78′ በደደቢት ሳጥን የቀኝ ክፍል ላይ አስቻለው ከኤልያስ የተቀበለውን ኳስ በፍጥነት ይዞ ለመግባት ሲሞክር ኳሷ ረዝማበት በአግባቡ መቆጣጠር ሳይችል ቀርቶ ወደውጪ ወጥታበታለች ።

76′ የኢትዮጵያ ቡና አማካዮች ተቀራርበው ኳስ በመቀባበል ወደ ደደቢት የግብ ክልል ለመግባት የሚያደርጉት ሙከራ በደደቢት ጠንካራ የመከላከል መስመር እየተመከተባቸው ነው ።

74′ የተጨዋች ለውጥ ኢትዮጵያ ቡና

አክሊሉ ዋለልኝ ወጥቶ አማኑኤል ዮሀንስ ገብቷል ።

71′ የተጨዋች ለውጥ ደደቢት 

ሮበን ኦባማ ዳዊት ፍቃዱን በመተካት ወደሜዳ ገብቷል ።

67′ ሳሙኤል ሳኑሚ ከደደቢቶች ሳጥን ጠርዝ ላይ ከኤልያስ ማሞ የተቀበለውን ኳስ አይናለም ኃይለን በማለፍ ከክሌመንት ጋር ብቻውን ተገናኝቶ ቢሞክርም በሚያስገርም ሁኔታ ኢላማውን መጠበቅ ሳይችል ቀርቷል። 
65′ ቡናማዎቹ ጫና ፈጥረው እየተጫወቱ ይገኛሉ ። አብዛኛው የጨዋታ እንቅስቃሴም በደደቢቶች ሜዳ ላይ ሆኗል ።

62′ አህመድ ረሻድ በደደቢቶች ፍፁም ቅጣት ምት ክልል ውስጥ ከመሀል ተከላካዩ አክሊሉ አያነው የነጠቀውን ኳስ ከቅርብ ርቀት አክርሮ ቢሞክርም ኳሷ የግቡን አግዳሚ ውስጠኛ ክፍል ለትማ ወጥታለች ። ከእስካሁኖቹ ሙከራዎች በጣሙን ለጎል የቀረበ አጋጣሚ !

59′ አህመድ ረሻድ ከግራ መስመር በመነሳት ለአስቻለው ያሳለፈለትን ኳስ አስቻለው ቢሞክርም ኳሷ በአግዳሚው ወደላይ ወጥታለች ።

57′ ኤልያስ እና እያሱ የተቀባበሉት ኳስ ሳኑሚ ጋር ደርሶ አጥቂው ከሳጥን ውጪ ቢሞክርም ክሌመንት ይዞበታል ።

55′ ከመጀመሪያው አጋማሽ ጀምሮ አሁንም የተጨዋቾች ግጭት እየተመለከትን ነው ። አልቢትሩ እስካሁን ካርድ ከማሳየት መቆጠባቸው በተለይ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎችን ደስተኛ አላደረገም ።

52′ የተጨዋች ለውጥ ደደቢት

ኤፍሬም አሻሞ ወጥቶ አቤል ያለው ገብቷል

50′ የሁለተኛው አጋማሽ አጀማመር ከመጀመሪያው በተቃራኒ የተቀዛቀዘ ሆኗል ።

47′ ጋቶች ፓኖም ከእያሱ ታምሩ ጋር መሀል ሜዳ ላይ ተቀባብሎ ወደፊት በመጠጋት ከረጅም ርቀት የሞከራው ኳስ ወደላይ በመነሳት በግቡ አናት ወጥቷል ።

46′ ሁለተኛው አጋማሽ በሳሙኤል ሳኑሚ አማካይነት ተጀምሯል ።

እረፍት!!

የመጀመርያው አጋማሽ ያለ ግብ ተጠናቋል፡፡

45 ‘ ጭማሪ ደቂቃ 2 !

43′ ቡናዎች በቀኝ መስመር የሰነዘሩትን ጥቃት ተከትሎ ሳኑሚ ወደውስጥ የላካትን ኳስ መጠቀም አልቻሉም ።

42′ ሰማያዊዎቹ በኢትዮጵያ ቡና ሜዳ ላይ ጫና ለመፍጠር ቢሞክሩም ከመስመር የሚያሻሟቸው ኳሶች በቀላሉ በሀሪሰን እጆች መሀል እየገቡ ነው ።

40′ አሁን ጨዋታው ሙሉ ለሙሉ በመሀል ሜዳ ላይ እንቅስቃሴ የተገደበ ሆኗል ።

35′ የሁለቱም ቡድኖች የማጥቃት ሂደቶች ሶስተኛው የሜዳ ክፍል ላይ ሲደርሱ እየተቋረጡ ይገኛሉ ።

33′ የግብ ሙከራዎች ቁትር ቢቀንስም ጨዋታው ከፍተኛ የተጨዋቾች ሽኩቻ እያስተናገደ ነው። ኢንተርናሽናል አልቢትር ኃይለየሱስ ባዘዘውም ካርድ ሳይመዙ ተጨዋቾችን በማረጋጋት ጨዋታውን ለመቆጣጠር እየሞከሩ ነው ።

30′ የተጨዋቾች ግጭት በጨዋታው እየተበራከተ ነው ።

27′ መሀል ሜዳ ላይ ከእያሱ የተቀበለውን ኳስ የክሌመንትን መውጣት በማየት ሳኑሚ በረጅሙ ወደጎል ቢሞክርም ኳስ በግቡ ​ወጥታለች ።

26′ ኤልያስ ማሞ በግራ መስመር የተገኘውን የማዕዘን ምት በአጭሩ ለአስቻለው ግርማ አቀብሎት ። አስቻለው በቀጥታ ሲሞክር ክሌመንት አድኖበታል ።

25 ‘ ኩሊባሊ ተነስቶ ጨዋታው ቀጥሏል ።

24′ ከድር ኩሊባሊ ጉዳት ደርሶበት የህክምና ዕርዳት እየተደረገለት በመሆኑ ጨዋታው ተቋርጧል ።

20′ በሁለቱ ቡድኖች መሀል ተመጣጣኝ እንቅስቃሴ እየተመለከትን እንገኛለን ።

19′ ሽመክት ጉግሳ ከቀኝ መስመር ያሻማውን ኳስ ጌታነህ ከበደ በግንባሩ በመግጨት ቢሞክርም ሀሪሰን ይዞበታል ።

15′ ጨዋታው ከመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች አንፃር ቀዝቀዝ ያለ ይመስላል ። ኢትዮጵያ ቡናዎችም እንደመጀመሪያው ወደግብ እየተጠጉ አይደለም ። ደደቢቶች ኳስ ተቆጣጥረው በተጋጣሚያቸው ሜዳ ላይ ለመቆየት ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ ።

13′ ዳዊት ፍቃዱ ከጌታነህ ከበደ ተነጥሎ እና ለአማካይ ክፍሉ በጣም ቀርቦ እየተጫወተ ይገኛል ። የተጨዋቹ ከወትሮው ቦታው የሚና ለውጥ ማድረጉ የኢትዮጵያ ቡናን የመሀል ክፍል የበላይነት ለመቀነስ የተደረገ ይመስላል ።

10′ እስካሁን ኢትዮጵያ ቡናዎች ዕድሎችን በመፍጠር የተሻሉ ሆነዋል ። የደደቢቶች ጥቃት አደጋ ለመፍጠር አቅም ያነሰው ይመስላል ።

9′ አህመድ ረሻድ ከግራ መስመር ያሻማውን ጥሩ ኳስ በጥሩ አቋቋም ላይ የነበረው ሳሙኤል ሳኑሚ በግንባሩ ቢሞክርም በግቡ አናት ወጥቶበታል ።

6′ ጋቶች ፓኖም ከኤልያስ ማሞ የተቀበለውን ኳስ ከረጅም ርቀት ቢሞክርም ወደላይ ወጥቶበታል ።

4′ ቡናዎች ከራሳቸው ግብ ላይ የነጠቁትን ኳስ በፈጣን መልሶ ማጥቃት ይዘው ወደደቢት የሜዳ ክፍል በአስቻለው ግርማ አማካይነት ይዘው ቢገቡም ከ አስቻለው ወደ አህመድ የተላከችው ኳስ በደደቢቶች ተነጥቃለች ።

1’ ኢትዮጵያ ቡና በቀኝ መስመር በአብዱልከሪም በኩል የሰነዘረው ጥቃት በሳሙኤል ሳኑሚ ወደ ውስጥ ቢሻገርም ኳሱን ለመጠቀም የተዘጋጀ ሰው ባለመኖሩ ውጤታማ መሆን አልቻለም ። ይሄው ጥቃት ቀጥሎም ኤልያስ ማሞ ከደደቢት ሳጥን ጠርዝ ላይ በቀጥታ የሞከረው ኳስ በግቡ ቋሚ ተመልሷል ። አደገኛ አጀማመር ! 

1′ ጨዋታው በደደቢቱ አጥቂ ጌታነህ ከበደ አማካይነት ተጀምሯል ።

09 ፡ 00 የቡድኖቹ ተጨዋቾች ወደሜዳ ገብተዋል ።

08 ፡ 55 የቡድኖቹ ተጨዋቾች ከመልበሻ ቤት እስኪወጡ በጉጉት እየጠበቁ ያሉት ደጋፊዎች በሕብረዝማሬ ስታድየሙን እያደመቁት ይገኛሉ ።

የኢትዮጵያ ቡና አሰላለፍ

99 ሀሪስን ሄሱ

15 አብዱልከሪም መሀመድ – 16 ኤፍሬም ወንድወሰን – 5 ወንድይፍራው ጌታሁን – 13 አህመድ ረሽድ 

9 ኤልያስ ማሞ  – 19 አክሊሉ ዋለልኝ – 25 ጋቶች ፓኖም

14 እያሱ ታምሩ – 11 ሳሙኤል ሳኑሚ – 24 አስቻለው ግርማ

ተጠባባቂዎች

29 ዮሃንስ በዛብህ

4 ኤኮ ፌቨር

28 ያቡን ዊልያም

17 አብዱልከሪም ሀሰን

3 መስዑድ መሀመድ

21 አስናቀ ሞገስ

8 አማኑኤል ዮሐንስ

የደደቢት አሰላለፍ

33 ክሌመንት አዞንቶ

15 ደስታ ደሙ – 6 አይናለም ኃይለ – 14 አክሊሉ አየነው – 10 ብርሃኑ ቦጋለ

 19 ሽመክት ጉግሳ – 8 ሳምሶን ጥላሁን  –  24 ኩሊባሊ ከድር– 21 ኤፍሬም አሻሞ 

9 ጌታነህ ከበደ – 17 ዳዊት ፍቃዱ

ተጠባባቂዎች

22 ታሪክ ጌትነት

16 ሰለሞን ሐብቴ

27 እያሱ ተስፋዬ

8 አስራት መገርሳ

18 አቤል እንዳለ

12 ሮበን ኦባማ

5 አንዳህ ኩዌኩ                                        

08 ፡ 45 ተጨዋቾቹ አሟሙቀው በመጨረስ ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል በመቀጠል የሁለቱን ቡድኖች አሰላለፍ ይዘን እንመለሳለን ።

08፡30 ተጨዋቾቹ ሰውነታቸውን ለማማሟቅ ወደ ሜዳ ገብተዋል ።

08 ፡ 20 ጨዋታው ሊጀመር 40 ደቂቃዎች ቢቀሩትም በተለምዶው ካታንጋ እና ዳፍ ትራክ ከሚባሉት ቦታዎች ውጪ የስቴድየሙ አብዛኛው ክፍል በደጋፊዎች ተሞልቷል ።

ዳኛ

የእለቱን ጨዋታ የ2007 የውድድር ዘመን ኮከብ ዳኛ ኢንተርናሽናል አርቢቴር ኃይለየሱስ ባዘዘው ይመራዋል ።

ያለፉት 3 ጨዋታዎች ውጤት

ኢትዮጵያ ቡና | አሸነፈ | አሸነፈ | አቻ

ደደቢት  | አቻ | ተሸነፈ | አሸነፈ

ግንኙነት

ሁለቱ ቡድኖች 15 ጊዜ ሲገናኙ ምንም ጊዜ አቻ ውጤት አላስመዘገቡም ። ደደቢት 9ኙን በማሸነፍ ቅድሚያ ሲይዝ ኢትዮጵያ ቡና ደግሞ በ6ቱ ድል ማድረግ ችሏል ። በነዚህ ግንኙነቶች ደደቢት 29 እንዲሁም ኢትዮጵያ ቡና 23 ግቦችን ማስቆጠር ችለዋል ።

ደረጃ

የኢትዮጵያ ቡና 24 ነጥቦችን በመሰብሰብ 6ኛ ደረጃ ላይ ሲገኝ ደደቢት በበኩሉ በ27 ነጥቦች ይዞ 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡

ጤና ይስጥልኝ ክቡራት እና ክቡራን !

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ሳምንት በጉጉት በሚጠበቀው  ታላቅ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡናን ከ ደደቢት የሚያገናኝ ይሆናል ። በአዲስ አበባ ስታድየም ከቀኑ 9 ሰዐት ጀምሮ የሚደረገውን የሁለቱን ቡድኖች ፍልሚያም በቀጥታ የፅሀፍ ስርጭት ልናስነብባችሁ ተዘጋጅተናል !

መልካም ቆይታ ከሶከር ኢትዮጵያ ጋር !

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *