ከሜይ 12 እስከ ጁን 4 በሱዳን አስተናጋጅነት የሚካሄደው የሴካፋ ናይል ቤዚን ዋንጫ የምድብ ድልድል ይፋ ሆኗል፡፡ 16 የሀገር ውስጥ የጥሎ ማለፍ አሸናፊዎች እና በሊግ ውድድር ከቻምፒዮንስ ሊግ ደረጃ ዝቅ ባለ ደረጃ የጨረሱ ክለቦችን የሚያሳትፈው ይኸው ውድድር ላይ የሚካፈለው የ2005 የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊው መከላከያ በምድብ ሶስት ከሱዳኑ አህሊ ሼንዲ ፣ ከግብፁ አል ማስሪ እና ከጅቡቲው ድኪህል ጋር ተደልድሏል፡፡
መከላከያ ለዚህ ውድድር ሲባል የሊጉን የ19ኛ ሳምንት ጨዋታ ቀደም ብሎ የተጫወተ ሲሆን የ20ኛ ሳምንት ጨዋታውን በመጪው አርብ ለማድረግ እያንገራገረ ይገኛል፡፡
የናይል ቤዚን ዋንጫ የምድብ ድልድል ይህንን መስላል፡-
ምድብ 1
አል-ሜሪክ – ሱዳን
ቪክቶርያ ዩኒቨርሲቲ – ዩጋንዳ
ማላኪያ – ደቡብ ሱዳን
ፖሊሲ – ዛንዚባር
ምድብ 2
አል-ሜሪክ አል ፋስር – ሱዳን
መዬባ ሲቲ – ታንዛንያ
ኤልማን – ሶማልያ
ሊዮፓርድስ – ኬንያ
ምድብ 3
አህሊ ሼንዲ – ሱዳን
አል-ማስር – ግብፅ
መከላከያ – ኢትዮጵያ
ድኪህል – ጅቡቲ
ምድብ 4
ሄይ አል አረብ – ሱዳን
አረብ ኮንትራክት – ግብፅ
ፍላምቢዩ ደ ልስት – ቡሩንዲ
ኤቲንሴሌስ – ሩዋንዳ
{jcomments on}