የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ላይ ባሉት ተስተካካይ ጨዋታዎች ምክንያት ቀጣይ ጨዋታዎች ላይ መሸጋሸግ ተደርጓል፡፡
በምድብ ሀ 23ኛ ሳምንት መቀለ ከተማ ከ ባህርዳር ከተማ የተቋረጠው ጨዋታ እንዲሁም በ28ኛ ሳምንት ላይ ሳይደረጉ የቀሩት የአማራ ውሀ ስራ እና መቀለ ከተማ ፤ የባህርዳር ከተማ እና ሽረ እንዳስላሴ ጨዋታዎች ከዚህ በታች ባሉት ቀናት እንደሚደረጉ የኢትየጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ያወጣው መርሀግብር ያሳያል፡-
ረቡዕ ሰኔ 21 ቀን 2009
04:00 መቀለ ከተማ ከ ባህርዳር ከተማ (አአ ስታድየም)
እሁድ ሰኔ 25 ቀን 2009
08:00 ባህርዳር ከተማ ከ ሽረ እንዳስላሴ (አአ ስታድየም)
10:00 አማራ ውሀ ስራ ከ መቀለ ከተማ (አአ ስታድየም)
ከላይ በተጠቀሱት ጨዋታዎች ምክንያት የተሻሻለው የ30ኛ ሳምንት መርሀ ግብር የሚከተለውን ይመስላል፡፡
*የወሎ ኮምቦልቻ እና ሽረ እንዳስላሴ ጨዋታ ሀሙስ ሰኔ 29 ይደረጋል
በምድብ ለ የሚደረጉት ሁለት ወሳኝ ጨዋታዎች ከምድብ ሀ ጋር በተመሳሳይ ጊዜ እንዲጠናቀቁ በሚል ወደ ሰኔ 29 ተገፍተዋል፡፡