የክልል ክለቦች ሻምፒዮና 6ኛ ቀን ውሎ
የኢትዮጵያ ክልል ክለቦች ሻምፒዮና ከአንድ ቀን እረፍት በኋላ አርብ በ8 ጨዋታዎች ቀጥሎ ሲካሄድ ወደ ሁለተኛው ዙር ያለፉ ተጨማሪ ክለቦችም ታውቀዋል፡፡
ምድብ 1
በዚህ ምድብ የተደረጉት ሁለት ጨዋታዎች በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል፡፡ ያሶ ከተማ ከ የጁ ፍሬ ወልዲያ ፣ ሾኔ ከተማ ከ ኢተያ ከተማ ያለግብ አቻ የተጠናቀቁ ጨዋታዎች ናቸው፡፡ ከምድቡ የጁ ፍሬ አስቀድሞ ማለፉን ማረጋገጡ የሚታወስ ሲሆን ሽረ እንዳስላሴ ቢ ከ ኢተያ ፣ ያሶ ከ ሾኔ የሚያደርጓቸው ወሳኝ ጨዋታዎች የጁን ተከትሎ የሚያልፈውን ቡድን ይለያል፡፡
ምድብ 2
በሙሀመድ ሁሴን አሊ አል–አሙዲን ስታድየም መርካቶ አካባቢን የገጠመው ድሬዳዋ ኮተን 3-2 በማሸነፍ ወደ ሁለተኛው ዙር ማለፉን አረጋግጧል፡፡
በ16ኛው ደቂቃ ከቀኝ መስመር የተሻገረውን ኳስ በድሉ ጆቢር በግምባር ገጭቶ መርካቶ አካባቢን ቀዳሚ ያደረገ ቢሆንም መሪነታቸው ግን መቆየት የቻለው ለ4 ደቂቃ ነበር፡፡ በ20ኛው ደቂቃ አብዱ አህመድ ወደ ሳጥን የተላከውን ኳስ በቺፕ አስቆጥሮ ኮተንን አቻ አድርጓል። በ24 ደቂቃ ደግሞ ከመሀል የተሻገረውን ሰንጣቂ ኳስ ተጠቅሞ ሳሙኤል ዘሪሁን ግብ ጠባቂውን አልፎ በማስቆጠር ኮተንን ወደ መሪነት አሸጋግሯል። ለእረፍት ሰንከንዶች በቀሩበት ሰአት ከቀኝ መስመር የተላከውን ኳስ አቤል ብርሀኑ አስቆጥሮ በሁለት አቻ ወደ መልበሻ ክፍል አምርተዋል።
መጎሻሸም በበዛበት ሁለተኛው አጋማሽ በ58 ደቂቃ ኄኖክ አበራ ከሳጥን ውጭ አክርሮ በመምታት ማራኪ ግብ አስቆጥሮ ኮተንን ለድል አብቅቷል፡፡
በዚህ ጨዋታ ኳስ አቀባይ በበቂ ሁኔታ ባለመኖሩ ተጫዋቾች ከሽቦ ውጭ ጭምር በመውጣት ኳስ ሲያመጡ ተስተውሏል።
በዚሁ ምድብ ቀጥሎ በተካሄደው ሌላ ጨዋታ ቤንች ማጂ ፖሊስ መተከል ፖሊስን 1-0 ማሸነፍ ችሏል፡፡ ከምድቡ ድሬዳዋ ኮተን ማለፉን በማረጋገጡ እኩል 4 ነግብ እና ተመሳሳይ የግብ ልዩነት ያላቸው መርካቶ ፣ ቤንችማጂ ፖሊስ እና ቡሬ ከተማ በመጨረሻው እለት ጨዋታ ወደ ተከታዩ ዙር የማለፍ እድላቸውን ይወስናሉ፡፡
ምድብ 3
ከዚህ ምድብ አስቀድሞ ማለፉን ያረጋገጠው ናኖ ሁርቡ በደጋን ከተማ 3-0 ሲሸነፍ አሳሳ ከተማ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ፖሊስን 3-2 በማሸነፍ ብዙ ባገባ በሚለው ደጋንን በመብለጥ ወደ ሁለተኛው ዙር መቀላቀል ችሏል፡፡
ምድብ 4
አረካ ከተማ ዋልያን 2-0 በመርታት ምድቡን በ1ኝነት ማጠናቀቁን ሲያረጋግጥ ሰንዳፋ በኬ ከ ነስር ክለብ ጋር 1-1 በመለያየት አረካን ተከትሎ ወደ 2ኛው ዙር አልፏል፡፡
ይህን ሊንክ ተጭነው ሙሉውን መርሀ ግብር ፣ ውጤት እና ሰንጠረዥ ያገኛሉ፡– የክልል ክለቦች ሻምፒዮና
About Post Author
Mohammed
ተዛማጅ ፅሁፎች
የሉሲዎቹ ዋና አሰልጣኝ ተጫዋቾችን ጠርተዋል
በዩጋንዳ ለሚደረገው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ23 ተጫዋቾችን ጥሪ አድርሷል፡፡ በዩጋንዳ ከግንቦት 24 ጀምሮ ለተከታታይ አስር ቀናት ለሚደረገው...
የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ውድድር ተራዘመ
የሴቶች ፕሪምየር ሊግ የሁለተኛው ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ተገፍቷል፡፡ የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታዎች በሀዋሳ ጅምራቸውን አድርገው...
የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ ተራዘመ
በዩጋንዳ አስተናጋጅነት የሚዘጋጀው የሴካፋ ሴቶች ዋንጫ የቀን ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ሉሲዎቹን ተሳታፊ የሚያደርገው የዘንድሮው የሴካፋ የሴቶች ዋንጫ በዩጋንዳ አስተናጋጅነት እንደሚደረግ ይጠበቃል፡፡...
“በእያንዳንዱ ጨዋታ የሚሰጠኝን ዕድል መጠቀም ላይ ነው እያተኮርኩ ያለሁት” ዳግም ተፈራ
በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ እየታዩ ካሉ ጥሩ ግብ ጠባቂዎች መካከል አንዱ ከሆነው ወጣት ጋር ቆይታ አድርገናል። የ2014 የቤትኪንግ የኢትዮጵያ...
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል
ከረፋድ አንስቶ ካዛንቺስ በሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሄድ የዋለው የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌደሬሽን አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ...
ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የዛሬ ጨዋታዎች ውሎ
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ፕሪምየር ሊግ የ17ኛ ሳምንት የመጀመርያ ቀን ጨዋታዎች ዛሬ ሲካሄዱ ሀዋሳ ከተማ ፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዲያ...
Average Rating